መጽሐፈ ኢዮብ 40
40
1እግዚአብሔርም መለሰ፥ ኢዮብንም እንዲህ አለው፦
2“በውኑ የሚከራከር ሰው
ሁሉን ከሚችል አምላክ ጋር ይከራከራልን?
ከእግዚአብሔር ጋር የሚዋቀስ እርሱ ይመልስለት።”#ግእዝ “ምስለ ቢጽከኑ ዘትትዋቀስ አንተ ከመ ትትዋሣእ እንዘ እግዚአብሔር ይዘልፈከ” ይላል።
የኢዮብ መልስ
3ኢዮብም መለሰ፥ እግዚአብሔርንም እንዲህ አለው፦
4“አንተ ስታስተምረኝ እኔ የምመልሰው ምን አለኝ?
ይህንስ እየሰማሁ ከእግዚአብሔር ጋር እከራከር ዘንድ እኔ ምንድን ነኝ?
እጄን በአፌ ላይ ከማኖር በቀር የምመልሰው ምንድን ነው?
5አንድ ጊዜ ተናገርሁ፥
ሁለተኛ ጊዜም ከእንግዲህ ወዲህ አልናገርም።”
እግዚአብሔር ለኢዮብ እንደ መለሰለት
6እግዚአብሔርም እንደገና በደመና ውስጥ ሆኖ ለኢዮብ መለሰለት፥ እንዲህም አለ፦
7“እንግዲህ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤
እጠይቅሃለሁ፥ አንተም መልስልኝ።
8ወይም ፍርዴን መቃወምህን ተው፥
ጽድቅህ እንድትገለጥ እንጂ እኔ በሌላ መንገድ የምፈርድብህ ይመስልሃልን?
9እንደ እግዚአብሔር ክንድ ያለ ክንድ አለህን?
ወይስ እንደ እርሱ ባለ ድምፅ ታንጐደጕዳለህን?
10እስኪ ልዕልናንና ኀይልን ተላበስ፤
በክብርና በግርማም ተጐናጸፍ።
11የቍጣህን መላእክት ላክ፤
ትዕቢተኛውንም ሁሉ አዋርደው።
12ትዕቢተኛውን ሰው ዝቅ ዝቅ አድርገው፤
ዝንጉዎችንም በአንድ ጊዜ አጥፋቸው።
13በአፈር ውስጥ በአንድነት ሰውራቸው፤
ፊታቸውንም በኀፍረት ሙላ።
14በዚያን ጊዜ ቀኝ እጅህ ታድንህ ዘንድ እንድትችል፥
እኔ ደግሞ እመሰክርልሃለሁ።
15“እነሆ፥ በአንተ ዘንድ የዱር አውሬ አለ፤
እንደ በሬ ሣር ይበላል።
16እነሆ፥ ብርታቱ በወገቡ ውስጥ ነው፤
ኀይሉም በሆዱ እንብርት ውስጥ ነው።
17ጅራቱን እንደ ጥድ ዛፍ ያወዛውዛል፤
የወርቹም ጅማት የተጐነጐነ ነው።
18የጐድን አጥንቱ እንደ ናስ ነው፤
የጀርባው አጥንቶችም እንደ ብረት ዘንጎች ናቸው።
19ይህ የእግዚአብሔር የፍጥረቱ አውራ ነው።
ከተፈጠረም በኋላ መላእክት ሣቁበት።#ዕብ. “ሠሪውም ሰይፍን ሰጠው” ይላል።
20 # በዕብራይስጥ ይለያል። ወደ ረዥም ተራራ በወጣ ጊዜም
በሜዳው ላሉ እንስሳት በጥልቁ ስፍራ ደስታን ያደርጋል።
21ጥላ ካለው ዛፍ በታች፥ በደንገል፥
በቄጠማና በሸንበቆ ሥር ይተኛል።
22ጥላ ያለው ዛፍ በጥላው ይሰውረዋል፤
የወንዝ አኻያ ዛፎችም ይከብቡታል።
23እነሆ፥ ወንዙ ቢጐርፍ አይደነግጥም፤
ዮርዳኖስም እስከ አፉ ድረስ ቢፈስስ እርሱ ይተማመናል።
24ዐይኑ እያየ በገመድ ይያዛልን?
አፍንጫውስ ይበሳልን?
25“በውኑ ዘንዶውን በመቃጥን ታወጣለህን?
በአፍንጫውስ ገመድ ታስራለህን?
26ወይስ ስናጋ በጕንጩ ታደርጋለህን?
ወይስ በችንካር ከንፈሩን ትበሳለህን?
27በውኑ ወደ አንተ እጅግ ይለምናልን?
በጣፈጠ ቃልስ ይናገርሃልን?
28በውኑ ከአንተ ጋር ቃል ኪዳን ይገባልን?
ወይስ ለዘለዓለም ባሪያ ይሆን ዘንድ ትወስደዋለህን?
29ከዎፍ ጋር እንደምትጫወት ከእርሱ ጋር ትጫወታለህን?
ወይስ እንደ ልጆች መጫወቻ ዎፍ ታስረዋለህን?
30 # በዕብራይስጥ ይለያል። አሕዛብ ይመገቡታልን?
ወይስ የፊንቄ ሰዎች ይካፈሉታልን?#ግእዝ “ወአሕዛብኒ ይትጋነዩ ሎቱ ...” ይላል።
31ጀልባዎች#ግእዝ “አዕዋፍ” ይላል። ሁሉ ቢሰበሰቡ የጅራቱን ቍርበት ሊሸከሙት አይችሉም።
አጥማጆችም ራሱን በመረብ መያዝ አይችሉም።
32እጅህን በላዩ ጫን፤
በአፉ#ግእዝ “በሥጋሁ” ይላል። የሚያደርገውን ጦርነት አስብ፥
እንግዲህም ወዲህ አትድገም፥
አላየህምን? ስለ እርሱስ የተባለውን አላደነቅህምን?
Currently Selected:
መጽሐፈ ኢዮብ 40: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ኢዮብ 40
40
1እግዚአብሔርም መለሰ፥ ኢዮብንም እንዲህ አለው፦
2“በውኑ የሚከራከር ሰው
ሁሉን ከሚችል አምላክ ጋር ይከራከራልን?
ከእግዚአብሔር ጋር የሚዋቀስ እርሱ ይመልስለት።”#ግእዝ “ምስለ ቢጽከኑ ዘትትዋቀስ አንተ ከመ ትትዋሣእ እንዘ እግዚአብሔር ይዘልፈከ” ይላል።
የኢዮብ መልስ
3ኢዮብም መለሰ፥ እግዚአብሔርንም እንዲህ አለው፦
4“አንተ ስታስተምረኝ እኔ የምመልሰው ምን አለኝ?
ይህንስ እየሰማሁ ከእግዚአብሔር ጋር እከራከር ዘንድ እኔ ምንድን ነኝ?
እጄን በአፌ ላይ ከማኖር በቀር የምመልሰው ምንድን ነው?
5አንድ ጊዜ ተናገርሁ፥
ሁለተኛ ጊዜም ከእንግዲህ ወዲህ አልናገርም።”
እግዚአብሔር ለኢዮብ እንደ መለሰለት
6እግዚአብሔርም እንደገና በደመና ውስጥ ሆኖ ለኢዮብ መለሰለት፥ እንዲህም አለ፦
7“እንግዲህ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤
እጠይቅሃለሁ፥ አንተም መልስልኝ።
8ወይም ፍርዴን መቃወምህን ተው፥
ጽድቅህ እንድትገለጥ እንጂ እኔ በሌላ መንገድ የምፈርድብህ ይመስልሃልን?
9እንደ እግዚአብሔር ክንድ ያለ ክንድ አለህን?
ወይስ እንደ እርሱ ባለ ድምፅ ታንጐደጕዳለህን?
10እስኪ ልዕልናንና ኀይልን ተላበስ፤
በክብርና በግርማም ተጐናጸፍ።
11የቍጣህን መላእክት ላክ፤
ትዕቢተኛውንም ሁሉ አዋርደው።
12ትዕቢተኛውን ሰው ዝቅ ዝቅ አድርገው፤
ዝንጉዎችንም በአንድ ጊዜ አጥፋቸው።
13በአፈር ውስጥ በአንድነት ሰውራቸው፤
ፊታቸውንም በኀፍረት ሙላ።
14በዚያን ጊዜ ቀኝ እጅህ ታድንህ ዘንድ እንድትችል፥
እኔ ደግሞ እመሰክርልሃለሁ።
15“እነሆ፥ በአንተ ዘንድ የዱር አውሬ አለ፤
እንደ በሬ ሣር ይበላል።
16እነሆ፥ ብርታቱ በወገቡ ውስጥ ነው፤
ኀይሉም በሆዱ እንብርት ውስጥ ነው።
17ጅራቱን እንደ ጥድ ዛፍ ያወዛውዛል፤
የወርቹም ጅማት የተጐነጐነ ነው።
18የጐድን አጥንቱ እንደ ናስ ነው፤
የጀርባው አጥንቶችም እንደ ብረት ዘንጎች ናቸው።
19ይህ የእግዚአብሔር የፍጥረቱ አውራ ነው።
ከተፈጠረም በኋላ መላእክት ሣቁበት።#ዕብ. “ሠሪውም ሰይፍን ሰጠው” ይላል።
20 # በዕብራይስጥ ይለያል። ወደ ረዥም ተራራ በወጣ ጊዜም
በሜዳው ላሉ እንስሳት በጥልቁ ስፍራ ደስታን ያደርጋል።
21ጥላ ካለው ዛፍ በታች፥ በደንገል፥
በቄጠማና በሸንበቆ ሥር ይተኛል።
22ጥላ ያለው ዛፍ በጥላው ይሰውረዋል፤
የወንዝ አኻያ ዛፎችም ይከብቡታል።
23እነሆ፥ ወንዙ ቢጐርፍ አይደነግጥም፤
ዮርዳኖስም እስከ አፉ ድረስ ቢፈስስ እርሱ ይተማመናል።
24ዐይኑ እያየ በገመድ ይያዛልን?
አፍንጫውስ ይበሳልን?
25“በውኑ ዘንዶውን በመቃጥን ታወጣለህን?
በአፍንጫውስ ገመድ ታስራለህን?
26ወይስ ስናጋ በጕንጩ ታደርጋለህን?
ወይስ በችንካር ከንፈሩን ትበሳለህን?
27በውኑ ወደ አንተ እጅግ ይለምናልን?
በጣፈጠ ቃልስ ይናገርሃልን?
28በውኑ ከአንተ ጋር ቃል ኪዳን ይገባልን?
ወይስ ለዘለዓለም ባሪያ ይሆን ዘንድ ትወስደዋለህን?
29ከዎፍ ጋር እንደምትጫወት ከእርሱ ጋር ትጫወታለህን?
ወይስ እንደ ልጆች መጫወቻ ዎፍ ታስረዋለህን?
30 # በዕብራይስጥ ይለያል። አሕዛብ ይመገቡታልን?
ወይስ የፊንቄ ሰዎች ይካፈሉታልን?#ግእዝ “ወአሕዛብኒ ይትጋነዩ ሎቱ ...” ይላል።
31ጀልባዎች#ግእዝ “አዕዋፍ” ይላል። ሁሉ ቢሰበሰቡ የጅራቱን ቍርበት ሊሸከሙት አይችሉም።
አጥማጆችም ራሱን በመረብ መያዝ አይችሉም።
32እጅህን በላዩ ጫን፤
በአፉ#ግእዝ “በሥጋሁ” ይላል። የሚያደርገውን ጦርነት አስብ፥
እንግዲህም ወዲህ አትድገም፥
አላየህምን? ስለ እርሱስ የተባለውን አላደነቅህምን?