1
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:17
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ እንዲከናወን አላደርግም፤ በአንቺ ላይ ለፍርድ የሚነሣውን ድምፅ ሁሉ ታጠፊያለሽ፤ ጠላቶችሽም ሁሉ ይፈረድባቸዋል፤ እግዚአብሔርንም ለሚያገለግሉ ርስት አላቸው፤ ጻድቃኔም ትሆኑኛላችሁ ይላል እግዚአብሔር።
Compare
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:17
2
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:10
ተራሮችን እንዳልቀሥፋቸው እንዳላፈልሳቸውም፥ ኮረብቶችም እንዳይነዋወጡ እንደ ማልሁ እንዲሁ ከእኔ ዘንድ ያለሽ ይቅርታ አያልቅም፤ የሰላምሽ ቃል ኪዳንም አይጠፋም፤ መሓሪሽ እግዚአብሔር ይህን ተናግሮአልና።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:10
3
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:4
አታፍሪምና አትፍሪ፤ አቷረጂምና አትደንግጪ፤ የዘለዓለም እፍረትሽንም ትረሺዋለሽ፤ የመበለትነትሽንም ስድብ ከእንግዲህ ወዲህ አታስቢም።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:4
4
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:5
ፈጣሪሽ እግዚአብሔር ነው፤ ስሙም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ የእስራኤልም አምላክ ታዳጊሽ ነው፤ እርሱም በምድር ሁሉ እንደዚሁ ይጠራል።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:5
5
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:2
የድንኳንሽን ስፍራ አስፊ፤ መጋረጃዎችሽንም ዘርጊ፤ አትቈጥቢ፤ አውታሮችሽን አስረዝሚ፤ ካስሞችሽንም ትከዪ።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:2
6
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:13
ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፤ ልጆችሽም በብዙ ሰላም ይኖራሉ።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:13
7
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:8
በጥቂት ቍጣ ፊቴን ከአንቺ ሰወርሁ፤ በዘለዓለም ቸርነት ይቅር እልሻለሁ፥ ይላል ታዳጊሽ እግዚአብሔር።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:8
8
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:7
ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፤ በታላቅ ምሕረትም ይቅር እልሻለሁ።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:7
9
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:9
ከኖኅ ዘመን ውኃ ጀምሮ ይህ ለእኔ ምስክር ነው፤ ቀድሞ ከእንግዲህ ወዲህ ምድርን እንዳልቈጣት እንደ ማልሁ፥
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:9
10
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:12
ግንብሽንም በቀይ ዕንቍ፥ በሮችሽንም ቢረሌ በተባለ ዕንቍ፥ ዳርቻዎችሽንም በከበረ ዕንቍ እሠራለሁ።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 54:12
Home
Bible
Plans
Videos