1
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:3-4
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
በክርክርና ከንቱ ውዳሴን በመውደድ አትሥሩ፤ ትሕትናን በያዘ ልቡና ከራሳችሁ ይልቅ ባልንጀራችሁን አክብሩ እንጂ አትታበዩ። ለባልንጀራችሁም እንጂ ለየራሳችሁ ብቻ አታስቡ።
Compare
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:3-4
2
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:5
ፍጹማን የሆናችሁ ሁላችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ እንደ አደረገልን ይህን አስቡ።
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:5
3
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:6-8
ይኸውም የእግዚአብሔር መልኩ ነው፤ ቀምቶ እግዚአብሔር የሆነ አይደለም። ነገር ግን የባርያን መልክ ይዞ፥ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ዝቅ አደረገ። እንደ ሰውም ሆኖ ራሱን አዋረደ፤ ለሞት እስከ መድረስም ታዘዘ፤ ሞቱም በመስቀል የሆነው ነው።
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:6-8
4
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:13
ለሚወደው ሥራ የሚረዳችሁ እርሱ እግዚአብሔር ይቅርታውን ይፈጽምላችሁ።
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:13
5
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:9-11
ስለዚህም እግዚአብሔር እጅግ ከፍ ከፍ አደረገው፤ ከስም ሁሉ የሚበልጥ ስምንም ሰጠው። ይህም በሰማይና በምድር በቀላያትና ከምድር በታች ያለ ጕልበት ሁሉ ለኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰግድ ዘንድ ነው። አንደበትም ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር አብ ክብር ጌታ እንደ ሆነ ያምን ዘንድ ነው።
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:9-11
6
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:14-15
የምትሠሩትን ሁሉ ያለ ማንጐራጐርና ያለ መጠራጠር በፍቅርና በስምምነት ሥሩ። እንደ እግዚአብሔር ልጆች ንጹሓንና የዋሃን ትሆኑ ዘንድ፥ በማያምኑና በጠማሞች ልጆች መካከል ነውር ሳይኖርባችሁ በዓለም እንደ ብርሃን ትታያላችሁ፤
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:14-15
7
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:12
አሁንም ወንድሞች ሆይ፥ ዘወትር እንደምትሰሙኝ ሳለሁ ብቻ ሳይሆን፥ ሳልኖርም በፍርሀትና በመንቀጥቀጥ ሆናችሁ ለድኅነታችሁ ሥሩ።
Explore ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 2:12
Home
Bible
Plans
Videos