ኢሳይያስ 18
18
በኢትዮጵያ ላይ የተነገረ ትንቢት
1በኢትዮጵያ#18፥1 የላይኛው የአባይ ወንዝ አካባቢን ያመላክታል። ወንዞች ዳር ለምትገኝ፣
ፉር ፉር የሚሉ ክንፎች ላሉባት#18፥1 ወይም፣ አንበጣ ማለት ነው። ምድር ወዮላት!
2ይህችውም መልእክተኞችን በባሕር፣
ከወንዞች ማዶ በደንገል ጀልባ የምትልክ ናት።
እናንተ ፈጣን መልእክተኞች
ረዣዥምና ቈዳው ወደ ለሰለሰ፣
ከቅርብም ከሩቅም ወደሚፈራ ሕዝብ፣
ኀያልና ቋንቋው ወደማይገባ፣
ወንዞች ምድሩን ወደሚከፍሉት መንግሥት፣ ሂዱ!
3እናንተ የዓለም ሕዝቦች፣
በምድርም የምትኖሩ ሁሉ፣
በተራሮች ላይ ምልክት ሲሰቀል ታዩታላችሁ፤
መለከትም ሲነፋ ትሰሙታላችሁ።
4 እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤
“ጸጥ ብዬ እቀመጣለሁ፤
ከማደሪያዬም በፀሓይ ሐሩር እንደሚያስፈልጋችሁ ብርቅርቅ ትኵሳት፣
በመከርም ሙቀት እንደ ደመና ጠል ሆኜ እመለከታለሁ።”
5ከመከር በፊት የአበባው ወቅት ሲያልፍ፣
አበባው የጐመራ የወይን ፍሬ ሲሆን፣
የወይን ሐረጉን ተቀጥላ በመግረዣ ይገርዘዋል፤
የተንሰራፋውንም ቅርንጫፍ ቈራርጦ ያስወግደዋልና።
6ሁሉም በተራራ ላይ ለሚኖሩ ነጣቂ አሞሮች፣
ለዱርም አራዊት ይተዋሉ፤
አሞሮች በጋውን ሁሉ ሲበሉት ይባጃሉ፤
የዱር አራዊትም ክረምቱን ሁሉ ሲበሉት ይከርማሉ።
7በዚያ ጊዜ ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር፣
ረዣዥምና ቈዳው ከለሰለሰ፣
ከቅርብም ከሩቅም ከሚፈራ ሕዝብ፣
ኀያልና ቋንቋው ከማይገባ፣
ወንዞችም ምድሩን ከሚከፍሉት መንግሥት፣ ገጸ በረከት ይመጣለታል፤
ገጸ በረከቱም የሚመጣለት የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም ወዳለበት ወደ ጽዮን ተራራ ነው።
Currently Selected:
ኢሳይያስ 18: NASV
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
ኢሳይያስ 18
18
በኢትዮጵያ ላይ የተነገረ ትንቢት
1በኢትዮጵያ#18፥1 የላይኛው የአባይ ወንዝ አካባቢን ያመላክታል። ወንዞች ዳር ለምትገኝ፣
ፉር ፉር የሚሉ ክንፎች ላሉባት#18፥1 ወይም፣ አንበጣ ማለት ነው። ምድር ወዮላት!
2ይህችውም መልእክተኞችን በባሕር፣
ከወንዞች ማዶ በደንገል ጀልባ የምትልክ ናት።
እናንተ ፈጣን መልእክተኞች
ረዣዥምና ቈዳው ወደ ለሰለሰ፣
ከቅርብም ከሩቅም ወደሚፈራ ሕዝብ፣
ኀያልና ቋንቋው ወደማይገባ፣
ወንዞች ምድሩን ወደሚከፍሉት መንግሥት፣ ሂዱ!
3እናንተ የዓለም ሕዝቦች፣
በምድርም የምትኖሩ ሁሉ፣
በተራሮች ላይ ምልክት ሲሰቀል ታዩታላችሁ፤
መለከትም ሲነፋ ትሰሙታላችሁ።
4 እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤
“ጸጥ ብዬ እቀመጣለሁ፤
ከማደሪያዬም በፀሓይ ሐሩር እንደሚያስፈልጋችሁ ብርቅርቅ ትኵሳት፣
በመከርም ሙቀት እንደ ደመና ጠል ሆኜ እመለከታለሁ።”
5ከመከር በፊት የአበባው ወቅት ሲያልፍ፣
አበባው የጐመራ የወይን ፍሬ ሲሆን፣
የወይን ሐረጉን ተቀጥላ በመግረዣ ይገርዘዋል፤
የተንሰራፋውንም ቅርንጫፍ ቈራርጦ ያስወግደዋልና።
6ሁሉም በተራራ ላይ ለሚኖሩ ነጣቂ አሞሮች፣
ለዱርም አራዊት ይተዋሉ፤
አሞሮች በጋውን ሁሉ ሲበሉት ይባጃሉ፤
የዱር አራዊትም ክረምቱን ሁሉ ሲበሉት ይከርማሉ።
7በዚያ ጊዜ ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር፣
ረዣዥምና ቈዳው ከለሰለሰ፣
ከቅርብም ከሩቅም ከሚፈራ ሕዝብ፣
ኀያልና ቋንቋው ከማይገባ፣
ወንዞችም ምድሩን ከሚከፍሉት መንግሥት፣ ገጸ በረከት ይመጣለታል፤
ገጸ በረከቱም የሚመጣለት የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም ወዳለበት ወደ ጽዮን ተራራ ነው።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.