መዝሙር 26
26
መዝሙር 26
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ነቀፋ እንደ መሆኔ፣
አንተው ፍረድልኝ።
ወዲያ ወዲህ ሳልልም፣
በእግዚአብሔር ታምኛለሁ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈትነኝ፤ መርምረኝም፤
ልቤንና ውስጤን መርምር፤
3ምሕረትህ ከፊቴ አልተለየምና፣
በእውነትህም ተመላለስሁ።
4ከማይረቡ ጋራ አልተቀመጥሁም፤
ከግብዞችም ጋራ አልተባበርሁም።
5የክፉዎችን ማኅበር ተጸየፍሁ፤
ከዐመፀኞችም ጋራ አልቀመጥም።
6እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ መሠዊያህንም እዞራለሁ፤
7የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣
ታምራትህንም አወራ ዘንድ ነው።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ የምትኖርበትን ቤት፣
የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።
9ነፍሴን ከኀጢአተኞች ጋራ፣
ሕይወቴንም ከደም አፍሳሾች ጋራ አታስወግዳት።
10በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ፤
ቀኝ እጃቸውም ጕቦን ያጋብሳል።
11እኔ ግን በተአማኒ ሕይወት እጓዛለሁ፤
አድነኝ፤ ምሕረትንም አድርግልኝ።
12እግሮቼ በደልዳላ ስፍራ ቆመዋል፤
በታላቅ ጉባኤ መካከልም እግዚአብሔርን እባርከዋለሁ።
Currently Selected:
መዝሙር 26: NASV
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 26
26
መዝሙር 26
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ነቀፋ እንደ መሆኔ፣
አንተው ፍረድልኝ።
ወዲያ ወዲህ ሳልልም፣
በእግዚአብሔር ታምኛለሁ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈትነኝ፤ መርምረኝም፤
ልቤንና ውስጤን መርምር፤
3ምሕረትህ ከፊቴ አልተለየምና፣
በእውነትህም ተመላለስሁ።
4ከማይረቡ ጋራ አልተቀመጥሁም፤
ከግብዞችም ጋራ አልተባበርሁም።
5የክፉዎችን ማኅበር ተጸየፍሁ፤
ከዐመፀኞችም ጋራ አልቀመጥም።
6እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ መሠዊያህንም እዞራለሁ፤
7የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣
ታምራትህንም አወራ ዘንድ ነው።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ የምትኖርበትን ቤት፣
የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።
9ነፍሴን ከኀጢአተኞች ጋራ፣
ሕይወቴንም ከደም አፍሳሾች ጋራ አታስወግዳት።
10በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ፤
ቀኝ እጃቸውም ጕቦን ያጋብሳል።
11እኔ ግን በተአማኒ ሕይወት እጓዛለሁ፤
አድነኝ፤ ምሕረትንም አድርግልኝ።
12እግሮቼ በደልዳላ ስፍራ ቆመዋል፤
በታላቅ ጉባኤ መካከልም እግዚአብሔርን እባርከዋለሁ።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.