መጽሐፈ መዝሙር 93
93
እግዚአብሔር ንጉሥ ነው
1እግዚአብሔር ንጉሥ ነው፤
ግርማንና ኀይልን ተጐናጽፎአል፤
ምድርን በአንድ ስፍራ አጸናት፤
ከቶም አትናወጥም።
2እግዚአብሔር ሆይ! ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው፤
አንተም ከዘመናት ሁሉ በፊት አምላክ ነህ።
3እግዚአብሔር ሆይ! ባሕሮች ይነሣሉ፤
ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው ይጮኻሉ፤
የሞገዳቸውም ድምፅ ይሰማል።
4ነገር ግን ድምፁ ከብዙ ውቅያኖሶች ድምፅ ይልቅ ታላቅ የሆነው
ከባሕር ማዕበሎችም የበረታው እግዚአብሔር፥
ከሁሉ የበለጠ ኀያል ነው።
5እግዚአብሔር ሆይ! ሕግህ ጽኑ ነው፤
መቅደስህም ለዘለዓለም ያማረና ቅዱስ ነው።
Currently Selected:
መጽሐፈ መዝሙር 93: አማ05
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997