YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙረ ዳዊት 100

100
1የምስጋና መዝሙር።
ምድር ሁሉ፥ ለጌታ እልል በሉ፥
2በደስታም ለጌታ ተገዙ፥
በእልልታም ወደ ፊቱ ግቡ።
3 # መዝ. 23፥1፤ 95፥7፤ ሚክ. 7፥14፤ ኢሳ. 64፥7። ጌታ እርሱ አምላክ እንደሆነ እወቁ፥
እርሱ ሠራን፥ እኛም የእርሱ ነን፥
እኛስ ሕዝቡ የማሰማርያውም በጎች ነን።
4 # መዝ. 106፥1፤ 107፥1፤ 118፥1፤ 136፥1፤ 138፥8፤ ኤር. 33፥11። ወደ ደጆቹ በውዳሴ፥
ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፥
አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፥
5ጌታ ቸር፥ ፍቅሩም ለዘለዓለም፥
እውነቱም ለልጅ ልጅ ነውና።

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in