1
የሉቃስ ወንጌል 5:4
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
ንግግሩንም ከጨረሰ በኋላ፥ ስምዖንን፦ “ወደ ጥልቁ ፈቀቅ በል፤ መረቦቻችሁንም ለማጥመድ ጣሉ፤” አለው።
Vergelijk
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:4
2
የሉቃስ ወንጌል 5:5-6
ስምዖንም መልሶ፦ “አቤቱ! ሌሊቱን ሙሉ ብንደክምም ምንም አልያዝንም፤ ነገር ግን በቃልህ መረቦቹን እጥላለሁ፤” አለው። ይህንም ባደረጉ ጊዜ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ፤ መረቦቻቸውም ተቀደዱ።
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:5-6
3
የሉቃስ ወንጌል 5:16
እርሱ ግን ገለል ብሎ ወደ በምድረ በዳዎች እየሄደ ይጸልይ ነበር።
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:16
4
የሉቃስ ወንጌል 5:32
ኀጢአተኞችን ወደ ንስሓ ልጠራ እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም።”
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:32
5
የሉቃስ ወንጌል 5:8
ስምዖን ጴጥሮስም ይህን ባየ ጊዜ በኢየሱስ ጉልበት ፊት ወድቆ፦ “ጌታ ሆይ! እኔ ኀጢአተኛ ሰው ነኝና ከኔ ራቅ፤” አለው።
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:8
6
የሉቃስ ወንጌል 5:31
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ “ሕመምተኞች እንጂ ጤነኞች ሐኪም አያስፈልጋቸውም፤
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:31
7
የሉቃስ ወንጌል 5:11
ታንኳዎቹንም ወደ ምድር አድርሰው ሁሉን ትተው ተከተሉት።
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:11
8
የሉቃስ ወንጌል 5:12-13
ከከተማዎችም በአንዲቱ ሳለ፥ እነሆ፥ ለምጽ የወረሰው አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስንም ባየው ጊዜ በግንባሩ ተደፍቶ፦ “ጌታ ሆይ! ብትፈቅድስ ልታነጻኝ ትችላለህ፤” ሲል ተማጸነው። እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና፦ “እፈቅዳለሁ፤ ንጻ፤” አለው፤ ወዲያውም ለምጹ ለቀቀው።
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:12-13
9
የሉቃስ ወንጌል 5:15
ስለ እርሱ የሚባለው ግን ይበልጡን በስፋት ተሰራጨ፤ ብዙ ሕዝብም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ይሰበሰቡ ነበር፤
Ontdek የሉቃስ ወንጌል 5:15
Thuisscherm
Bijbel
Leesplannen
Video's