መዝሙር 108
108
መዝሙር 108
108፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 57፥7-11
108፥6-13 ተጓ ምብ – መዝ 60፥5-12
የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።
1አምላክ ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤
እቀኛለሁ፤ በፍጹም ነፍሴም እዘምራለሁ።
2በገናና መሰንቆም ተነሡ፤
እኔም ማልጄ እነሣለሁ።
3 ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤
በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ።
4ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና፤
ታማኝነትህም እስከ ሰማያት ትደርሳለች።
5አምላክ ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤
ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትንሰራፋ።
6ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣
በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስልንም።
7እግዚአብሔር ከመቅደሱ ተናገረ፤
“ደስ እያለኝ ሴኬምን እከፋፍላለሁ፤
የሱኮትንም ሸለቆ እለካለሁ።
8ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤
ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤
ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።
9ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤
በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤
በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እጮኻለሁ።”
10ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል?
ወደ ኤዶምያስ ማን ይመራኛል?
11እግዚአብሔር ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?
አምላክ ሆይ፤ ከሰራዊታችንም ጋራ አትወጣም።
12በጠላት ላይ ድልን አቀዳጀን፤
የሰው ርዳታ ከንቱ ነውና።
13በእግዚአብሔር ክንደ ብርቱ እንሆናለን፤
ጠላቶቻችንን የሚረጋግጥልን እርሱ ነውና።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 108
108
መዝሙር 108
108፥1-5 ተጓ ምብ – መዝ 57፥7-11
108፥6-13 ተጓ ምብ – መዝ 60፥5-12
የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።
1አምላክ ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤
እቀኛለሁ፤ በፍጹም ነፍሴም እዘምራለሁ።
2በገናና መሰንቆም ተነሡ፤
እኔም ማልጄ እነሣለሁ።
3 ጌታ ሆይ፤ በሕዝቦች መካከል አመሰግንሃለሁ፤
በሰዎችም መካከል እዘምርልሃለሁ።
4ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና፤
ታማኝነትህም እስከ ሰማያት ትደርሳለች።
5አምላክ ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤
ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትንሰራፋ።
6ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣
በቀኝ እጅህ ርዳን፤ መልስልንም።
7እግዚአብሔር ከመቅደሱ ተናገረ፤
“ደስ እያለኝ ሴኬምን እከፋፍላለሁ፤
የሱኮትንም ሸለቆ እለካለሁ።
8ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤
ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤
ይሁዳም በትረ መንግሥቴ ነው።
9ሞዓብ የመታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤
በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤
በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እጮኻለሁ።”
10ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል?
ወደ ኤዶምያስ ማን ይመራኛል?
11እግዚአብሔር ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?
አምላክ ሆይ፤ ከሰራዊታችንም ጋራ አትወጣም።
12በጠላት ላይ ድልን አቀዳጀን፤
የሰው ርዳታ ከንቱ ነውና።
13በእግዚአብሔር ክንደ ብርቱ እንሆናለን፤
ጠላቶቻችንን የሚረጋግጥልን እርሱ ነውና።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.