መዝሙር 114
114
መዝሙር 114
1እስራኤል ከግብጽ ወጥቶ ሲሄድ፣
የያዕቆብም ቤት ቋንቋው ልዩ ከሆነ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ፣
2ይሁዳ የእግዚአብሔር መቅደስ፣
እስራኤልም ግዛቱ ሆነ።
3ባሕር አየች፤ ሸሸችም፤
ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።
4ተራሮች እንደ አውራ በግ፣
ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ።
5አንቺ ባሕር፤ የሸሸሽው አንቺም ዮርዳኖስ ያፈገፈግሽው ለምንድን ነው?
6እናንተ ተራሮች እንደ አውራ በግ፣
ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ለምን ዘለላችሁ?
7ምድር ሆይ፤ በጌታ ፊት፣
በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፤
8እርሱ ዐለቱን ወደ ኵሬ፣
ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 114
114
መዝሙር 114
1እስራኤል ከግብጽ ወጥቶ ሲሄድ፣
የያዕቆብም ቤት ቋንቋው ልዩ ከሆነ ሕዝብ ተለይቶ ሲወጣ፣
2ይሁዳ የእግዚአብሔር መቅደስ፣
እስራኤልም ግዛቱ ሆነ።
3ባሕር አየች፤ ሸሸችም፤
ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ።
4ተራሮች እንደ አውራ በግ፣
ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ።
5አንቺ ባሕር፤ የሸሸሽው አንቺም ዮርዳኖስ ያፈገፈግሽው ለምንድን ነው?
6እናንተ ተራሮች እንደ አውራ በግ፣
ኰረብቶችም እንደ ጠቦት ለምን ዘለላችሁ?
7ምድር ሆይ፤ በጌታ ፊት፣
በያዕቆብ አምላክ ፊት ተንቀጥቀጪ፤
8እርሱ ዐለቱን ወደ ኵሬ፣
ቋጥኙንም ወደ ውሃ ምንጭ ለወጠ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.