መዝሙር 124
124
መዝሙር 124
የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።
1እስራኤል እንዲህ ይበል፤
እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣
2ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፣
እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣
3ቍጣቸው በላያችን በነደደ ጊዜ፣
በቁመናችን በዋጡን ነበር፤
4ጐርፍ ባጥለቀለቀን፣
ፈረሰኛው ውሃ ባሰጠመን፣
5ደራሽ ውሃም ጠራርጎ በወሰደን ነበር።
6በጥርሳቸው ከመዘንጠል የጠበቀን፣
እግዚአብሔር ይባረክ።
7ነፍሳችን እንደ ወፍ፣
ከዐዳኝ ወጥመድ አመለጠች፤
ወጥመዱ ተሰበረ፤
እኛም አመለጥን።
8የሰማይና የምድር ፈጣሪ፣
የእግዚአብሔር ስም ረዳታችን ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 124
124
መዝሙር 124
የዳዊት መዝሙረ መዓርግ።
1እስራኤል እንዲህ ይበል፤
እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣
2ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፣
እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ባይሆን ኖሮ፣
3ቍጣቸው በላያችን በነደደ ጊዜ፣
በቁመናችን በዋጡን ነበር፤
4ጐርፍ ባጥለቀለቀን፣
ፈረሰኛው ውሃ ባሰጠመን፣
5ደራሽ ውሃም ጠራርጎ በወሰደን ነበር።
6በጥርሳቸው ከመዘንጠል የጠበቀን፣
እግዚአብሔር ይባረክ።
7ነፍሳችን እንደ ወፍ፣
ከዐዳኝ ወጥመድ አመለጠች፤
ወጥመዱ ተሰበረ፤
እኛም አመለጥን።
8የሰማይና የምድር ፈጣሪ፣
የእግዚአብሔር ስም ረዳታችን ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.