መዝሙር 127
127
መዝሙር 127
የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ።
1 እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፣
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፣
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።
2የዕለት ጕርስ ለማግኘት በመጣር፣
ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣
አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤
እርሱ ለሚወድዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።#127፥2 ወይም ተኝተው ሳሉ ምግብ ያዘጋጅላቸዋል።
3እነሆ፤ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤
የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።
4በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣
በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።
5ብፁዕ ነው፤
ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ ሰው፤
ከጠላቶቻቸው ጋራ በአደባባይ በሚሟገቱበት ጊዜ፣
አይዋረዱም።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 127
127
መዝሙር 127
የሰሎሞን መዝሙረ መዓርግ።
1 እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፣
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፣
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል።
2የዕለት ጕርስ ለማግኘት በመጣር፣
ማልዳችሁ መነሣታችሁ፣
አምሽታችሁም መተኛታችሁ ከንቱ ነው፤
እርሱ ለሚወድዳቸው እንቅልፍን ያድላልና።#127፥2 ወይም ተኝተው ሳሉ ምግብ ያዘጋጅላቸዋል።
3እነሆ፤ ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው፤
የማሕፀንም ፍሬ ከቸርነቱ የሚገኝ ነው።
4በወጣትነት የተገኙ ወንዶች ልጆች፣
በጦረኛ እጅ እንዳሉ ፍላጾች ናቸው።
5ብፁዕ ነው፤
ኰረጆዎቹ በእነዚህ የተሞሉ ሰው፤
ከጠላቶቻቸው ጋራ በአደባባይ በሚሟገቱበት ጊዜ፣
አይዋረዱም።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.