መዝሙር 150

150
መዝሙር 150
1ሃሌ ሉያ።#150፥1 አንዳንዶች ከ6 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።
እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤
በታላቅ ጠፈሩ አመስግኑት።
2ስለ ብርቱ ሥራው አመስግኑት፤
እጅግ ታላቅ ነውና አመስግኑት።
3በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤
በበገናና በመሰንቆ ወድሱት።
4በከበሮና በሽብሸባ አመስግኑት፤
በባለአውታር መሣሪያና በእንቢልታ አመስግኑት።
5ተርገብጋቢ ድምፅ ባለው ጸናጽል አመስግኑት፤
ድምፀ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት።
6እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን።
ሃሌ ሉያ።

Currently Selected:

መዝሙር 150: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ