መዝሙር 2

2
መዝሙር 2
1አሕዛብ ለምን በቍጣ ተነሣሡ?
ሕዝቡስ ለምን በከንቱ አሤሩ?#2፥1 ዕብራይስጡ እንዲሁ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን ይቈጣሉ ይላል።
2የምድር ነገሥታት ተነሡ፤
ገዦችም በእግዚአብሔርና በመሲሑ#2፥2 ወይም የተቀባው ላይ
ሊመክሩ ተሰበሰቡ፤
3“ሰንሰለታቸውን እንበጥስ፣
የእግር ብረታቸውንም አውልቀን እንጣል” አሉ።
4በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ይሥቃል፤
ጌታም ይሣለቅባቸዋል።
5ከዚያም በቍጣው ይናገራቸዋል፤
በመዓቱም ያስደነግጣቸዋል፤
6ደግሞም፣ “እኔ ግን በተቀደሰው ተራራዬ፣
በጽዮን ላይ የራሴን ንጉሥ ሾምሁ” ይላል።
7እግዚአብሔርን ሕግ ዐውጃለሁ፤
እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “አንተ ልጄ ነህ፤
እኔ ዛሬ ወለድሁህ፤#2፥7 ወይም …አባትህ ሆንሁ
8ለምነኝ፤
መንግሥታትን ርስት አድርጌ፣
የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሃለሁ።
9አንተም በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ፤#2፥9 ወይም በብረት ዘንግ ትሰባብራቸዋለህ
እንደ ሸክላ ዕቃ ታደቅቃቸዋለህ።”
10ስለዚህ እናንተ ነገሥታት ልብ በሉ፤
እናንተ የምድር ገዦችም፣ ተጠንቀቁ።
11 እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤
ለርሱ በመንቀጥቀጥ ደስ ያሰኛችሁ።
12እንዳይቈጣና በመንገድ እንዳትጠፉ፣
ዝቅ ብላችሁ ልጁን ሳሙት፤
ቍጣው ፈጥኖ ይነድዳልና።
እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ ብፁዓን ናቸው።

Currently Selected:

መዝሙር 2: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ