መዝሙር 29
29
መዝሙር 29
የዳዊት መዝሙር።
1እናንተ ኀያላን፣ ለእግዚአብሔር ስጡ፤
ክብርንና ብርታትን ለእግዚአብሔር ስጡ።
2ለስሙ የሚገባ ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤
በቅድስናው ግርማ ለእግዚአብሔር ስገዱ።
3የእግዚአብሔር ድምፅ በውሆች ላይ ነው፤
የክብር አምላክ አንጐደጐደ፤
እግዚአብሔር በታላላቅ ውሆች ላይ አንጐደጐደ።
4የእግዚአብሔር ድምፅ ኀያል ነው፤
የእግዚአብሔር ድምፅ ግርማዊ ነው።
5የእግዚአብሔር ድምፅ ዝግባን ይሰብራል፤
እግዚአብሔር የሊባኖስን ዝግባ ይሰባብራል።
6ሊባኖስን እንደ ጥጃ፣
ሢርዮንንም#29፥6 አርሞንዔም የተባለው ተራራ ነው። እንደ አውራሪስ ግልገል ያዘልላል።
7የእግዚአብሔር ድምፅ
የእሳት ነበልባል ይረጫል።
8የእግዚአብሔር ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፤
የእግዚአብሔር ድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል።
9የእግዚአብሔር ድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል፤#29፥9 ወይም እግዚአብሔር አጋዘን እንድትወልድ ያደርጋል
ጫካዎችንም ይመነጥራል፤
ሁሉም በርሱ ቤተ መቅደስ ሆኖ “ይክበር!” ይላል።
10 እግዚአብሔር በጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጧል፤#29፥10 ወይም ይቀመጣል
እግዚአብሔር በንጉሥነቱ ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ይቀመጣል።
11 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታትን ይሰጣል፤
እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.