መዝሙር 67
67
መዝሙር 67
ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።
1እግዚአብሔር ይማረን፤ ይባርከን፤
ፊቱንም በላያችን ያብራ፤ ሴላ
2መንገድህ በምድር ላይ፣
ማዳንህም በሕዝቦች ሁሉ መካከል ይታወቅ ዘንድ።
3እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰዎች ያመስግኑህ፤
ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ።
4ለሕዝቦች በቅን ስለምትፈርድላቸው፣
ሰዎችንም በምድር ላይ ስለምትመራ፣
ሕዝቦች ደስ ይበላቸው፤ በእልልታም ይዘምሩ። ሴላ
5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰዎች ያመስግኑህ፤
ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ።
6ምድር ፍሬዋን ሰጠች፤
እግዚአብሔር፣ አምላካችን ይባርከናል።
7እግዚአብሔር ይባርከናል፤
የምድርም ዳርቻዎች ሁሉ እርሱን ይፈሩታል።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 67
67
መዝሙር 67
ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር፤ ማሕሌት።
1እግዚአብሔር ይማረን፤ ይባርከን፤
ፊቱንም በላያችን ያብራ፤ ሴላ
2መንገድህ በምድር ላይ፣
ማዳንህም በሕዝቦች ሁሉ መካከል ይታወቅ ዘንድ።
3እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰዎች ያመስግኑህ፤
ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ።
4ለሕዝቦች በቅን ስለምትፈርድላቸው፣
ሰዎችንም በምድር ላይ ስለምትመራ፣
ሕዝቦች ደስ ይበላቸው፤ በእልልታም ይዘምሩ። ሴላ
5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰዎች ያመስግኑህ፤
ሰዎች ሁሉ ምስጋና ያቅርቡልህ።
6ምድር ፍሬዋን ሰጠች፤
እግዚአብሔር፣ አምላካችን ይባርከናል።
7እግዚአብሔር ይባርከናል፤
የምድርም ዳርቻዎች ሁሉ እርሱን ይፈሩታል።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.