መዝሙር 82
82
መዝሙር 82
የአሳፍ መዝሙር።
1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤
በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤
2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?
ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ
3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ አደጎች ፍረዱላቸው፤
የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።
4ወገን የሌለውንና ድኻውን ታደጉ፤
ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።
5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤
በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤
የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።
6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤
ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።
7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤
እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”
8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣
ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 82
82
መዝሙር 82
የአሳፍ መዝሙር።
1እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤
በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፤
2“ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?
ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ
3ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ አደጎች ፍረዱላቸው፤
የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።
4ወገን የሌለውንና ድኻውን ታደጉ፤
ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።
5“ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤
በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤
የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።
6“እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤
ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።
7ነገር ግን እንደ ማንኛውም ሰው ትሞታላችሁ፤
እንደ ማንኛውም ገዥ ትወድቃላችሁ።”
8አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ በምድር ላይ ፍረድ፣
ሕዝቦች ሁሉ ርስትህ ናቸውና።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.