መዝሙር 97
97
መዝሙር 97
1 እግዚአብሔር ነገሠ፤ ምድር ደስ ይበላት፤
በሩቅ ያሉ የባሕር ጠረፎች ሐሤት ያድርጉ።
2ደመናና ጥቅጥቅ ያለ ጭጋግ በዙሪያው አለ፤
ጽድቅና ፍትሕ የዙፋኑ መሠረት ናቸው።
3እሳት በፊቱ ይሄዳል፤
በዙሪያው ያሉትንም ጠላቶቹን ይፈጃል።
4መብረቁ ዓለምን አበራ፤
ምድርም አይታ ተንቀጠቀጠች።
5ተራሮች በእግዚአብሔር ፊት፣
በምድርም ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም ቀለጡ።
6ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፤
ሕዝቦችም ሁሉ ክብሩን ያያሉ።
7ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ፣
በጣዖታትም የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ፤
እናንተ አማልክት ሁሉ፤ ለርሱ ስገዱ።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለ ፍርድህ፣
ጽዮን ሰምታ ደስ አላት፤
የይሁዳም ሴት ልጆች ሐሤት አደረጉ።
9 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና፤
ከአማልክትም ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ።
10 እግዚአብሔርን የምትወድዱ ክፋትን ጥሉ፤
እርሱ የታማኞቹን ነፍስ ይጠብቃልና፤
ከዐመፀኞችም እጅ ይታደጋቸዋል።
11ብርሃን ለጻድቃን፣
ሐሤትም ልባቸው ለቀና ወጣ።
12እናንተ ጻድቃን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤
ቅዱስ ስሙንም አመስግኑ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 97
97
መዝሙር 97
1 እግዚአብሔር ነገሠ፤ ምድር ደስ ይበላት፤
በሩቅ ያሉ የባሕር ጠረፎች ሐሤት ያድርጉ።
2ደመናና ጥቅጥቅ ያለ ጭጋግ በዙሪያው አለ፤
ጽድቅና ፍትሕ የዙፋኑ መሠረት ናቸው።
3እሳት በፊቱ ይሄዳል፤
በዙሪያው ያሉትንም ጠላቶቹን ይፈጃል።
4መብረቁ ዓለምን አበራ፤
ምድርም አይታ ተንቀጠቀጠች።
5ተራሮች በእግዚአብሔር ፊት፣
በምድርም ሁሉ ጌታ ፊት እንደ ሰም ቀለጡ።
6ሰማያት ጽድቁን ያውጃሉ፤
ሕዝቦችም ሁሉ ክብሩን ያያሉ።
7ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ፣
በጣዖታትም የሚመኩ ሁሉ ይፈሩ፤
እናንተ አማልክት ሁሉ፤ ለርሱ ስገዱ።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለ ፍርድህ፣
ጽዮን ሰምታ ደስ አላት፤
የይሁዳም ሴት ልጆች ሐሤት አደረጉ።
9 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና፤
ከአማልክትም ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ።
10 እግዚአብሔርን የምትወድዱ ክፋትን ጥሉ፤
እርሱ የታማኞቹን ነፍስ ይጠብቃልና፤
ከዐመፀኞችም እጅ ይታደጋቸዋል።
11ብርሃን ለጻድቃን፣
ሐሤትም ልባቸው ለቀና ወጣ።
12እናንተ ጻድቃን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤
ቅዱስ ስሙንም አመስግኑ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.