መዝሙረ ዳዊት 142
142
1ጸሎት፥ በዋሻ በነበረ ጊዜ፥ የዳዊት ትምህርት።
2በሙሉ ድምጼ ወደ ጌታ ጮኽሁ፥
በሙሉ ድምጼ ወደ ጌታ ለመንሁ።
3ሮሮዬን በፊቱ አፈስሳለሁ፥
መከራዬንም በፊቱ እናገራለሁ።
4 #
መዝ. 139፥24፤ 141፥9፤ 143፥4። መንፈሴ በዛለ ጊዜ መንገዴን አወቅሁ፥
በምሄድባት በዚያች መንገድ ወጥመድን ሰወሩብኝ።
5 #
መዝ. 16፥8፤ 73፥23፤ 121፥5። ወደ ቀኝ ተመለከትሁ አየሁም፥
የሚያውቀኝም አጣሁ፥
መሸሸጊያም የለኝም፥ ስለ ነፍሴም የሚያስብ የለም።
6 #
መዝ. 91፥2፤9፤ መዝ. 16፥5፤ 27፥13፤ 116፥9፤ ኢሳ. 38፥11። አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ፦
አንተ መጠጊያዬ ነህ፥
በሕያዋንም ምድር አንተ እድል ፈንታዬ ነህ አልሁ።
7 #
መዝ. 79፥8። እጅግ ተቸግሬአለሁና ጩኸቴን አድምጥ፥
በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።
8አቤቱ፥ ስምህን አመሰግን ዘንድ
ነፍሴን ከወህኒ አውጣት፥
ስለ ምታጠግበኝ
ጻድቃን እኔን ይከባሉ።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 142: መቅካእኤ
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መዝሙረ ዳዊት 142
142
1ጸሎት፥ በዋሻ በነበረ ጊዜ፥ የዳዊት ትምህርት።
2በሙሉ ድምጼ ወደ ጌታ ጮኽሁ፥
በሙሉ ድምጼ ወደ ጌታ ለመንሁ።
3ሮሮዬን በፊቱ አፈስሳለሁ፥
መከራዬንም በፊቱ እናገራለሁ።
4 #
መዝ. 139፥24፤ 141፥9፤ 143፥4። መንፈሴ በዛለ ጊዜ መንገዴን አወቅሁ፥
በምሄድባት በዚያች መንገድ ወጥመድን ሰወሩብኝ።
5 #
መዝ. 16፥8፤ 73፥23፤ 121፥5። ወደ ቀኝ ተመለከትሁ አየሁም፥
የሚያውቀኝም አጣሁ፥
መሸሸጊያም የለኝም፥ ስለ ነፍሴም የሚያስብ የለም።
6 #
መዝ. 91፥2፤9፤ መዝ. 16፥5፤ 27፥13፤ 116፥9፤ ኢሳ. 38፥11። አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ፦
አንተ መጠጊያዬ ነህ፥
በሕያዋንም ምድር አንተ እድል ፈንታዬ ነህ አልሁ።
7 #
መዝ. 79፥8። እጅግ ተቸግሬአለሁና ጩኸቴን አድምጥ፥
በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።
8አቤቱ፥ ስምህን አመሰግን ዘንድ
ነፍሴን ከወህኒ አውጣት፥
ስለ ምታጠግበኝ
ጻድቃን እኔን ይከባሉ።