መጽሐፈ ዕዝራ ካልእ 4
4
ስለ ንጉሥ አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
1ንጉሥ ያሸንፋል ያለው ሁለተኛውም ይናገር ጀመረ። 2“እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሰዎች ምድርን የሚያሸንፏት፥ ባሕርንም፥ በውስጧ ያለውንም ሁሉ የሚገዙ አይደለምን? 3ንጉሥም ለእነርሱ ጌታቸው ነው፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ነገር ግን ንጉሡ የበለጠ ኀይለኛ ነው” ይላል። ፈጽሞም ይገዛቸዋል፤ እርሱ ያዘዛቸውንም ሁሉ ያደርጋሉ። 4ባልንጀራችሁን ግደሉ ቢላቸውም ይገድላሉ ወደ ጦርነትም ሂዱ ቢላቸው ይሄዳሉ፤ ተራሮችንም ይንዳሉ፤ አጥሩንና ግንቡንም ያፈርሳሉ። 5የንጉሡንም ትእዛዝ እንቢ እንዳይሉ ይገድላሉ፤ ይገደላሉም፤ ድል ቢያደርጉም#ግእዙ “ወለእመ ሞዐ ንጉሥ” ይላል። የማረኩትን ምርኮ ሁሉ ለንጉሡ ያገባሉ።
6“ያልዘመቱና ያልተዋጉ፥ ምድርን የሚያርሱ እነርሱ ዘርተው አዝመራቸውን ባገቡ ጊዜ ግብሩን ለንጉሡ ይሰጣሉ። ለንጉሡም ግብር እንዲከፍል አንዱ ሌላውን ያስገድደዋል። 7እርሱ ግን አንድ ብቻ ነው፤ ግደሉ ቢላቸው ይገድላሉ፤ ተዉ ቢላቸውም ይተዋሉ። 8ግረፉ ቢላቸውም ይገርፋሉ፤ ገንቡ ቢላቸውም ይገነባሉ፤ አፍርሱ ቢላቸውም ያፈርሳሉ። 9ቍረጡ ቢላቸው ይቈርጣሉ፤ ትከሉ ቢላቸውም ይተክላሉ። 10ሕዝቡ ሁሉና ሠራዊቱም ላንድ ለእርሱ ይታዘዙለታል፤ ከዚህም ሁሉ ጋራ እርሱ ተቀምጦ በልቶና ጠጥቶ ይተኛል። 11ሌላውም ዙሪያውን ይጠብቃል፤ ከእነርሱም ተለይቶ ሄዶ ጉዳዩን ማድረግ የሚችል አንድም የለም፤ በማናቸውም ነገር እንቢ ይሉት ዘንድ አይችሉም። 12እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሁሉ እንዲህ የሚታዘዝለት ንጉሥ አያሸንፍምን?” ከዚህም በኋላ ዝም አለ።
ስለ ሴት አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
13ስለ ሴቶችና ስለ እውነት የተናገረው ሦስተኛውም ይናገር ጀመረ፤ እርሱም ዘሩባቤል ነው። እርሱም እንዲህ አለ፦ 14“እናንተ ሰዎችሆይ፥ ንጉሡ ታላቅ አይደለምን? ሰዎቹስ ብዙ አይደሉምን? ወይንስ ብርቱ አይደለምን? እኒህንስ የሚገዛቸውና የሚያዝዛቸው ማነው? ሴቶች አይደሉምን? 15ሴቶች ምድርንና ባሕርን የሚገዙ ንጉሡንና ሕዝቡን ሁሉ ወልደዋል። 16ከእነርሱም ተወለዱ፤ እነርሱም ከእርሱ ወይን የሚገኝበት የወይን ተክልን የሚተክሉ ሰዎችን አሳደጉ። 17እነርሱም ለሰዎች ልብስን ይሠራሉ፤ ለወንዶችም ክብርን ያደርጋሉ፤ ወንዶችም ያለ ሴት መኖር አይቻላቸውም። 18ሰዎች ምንም እንኳ ብሩንና ወርቁን፥ መልካሙንም ዕቃ ሁሉ ቢሰበስቡ፥ መልኳ ያማረና ደም ግባትዋ የተወደደ አንዲት ሴትን ባዩ ጊዜ፥ 19ያን ሁሉ ረስተው እርሷን ይመለከታሉ፤ አፏንም ያያሉ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አፋቸውን ከፍተው በትኩረት ይመለከትዋታል” ይላል። ሁሉም ያደንቋታል፤ ከወርቅና ከብር፥ ካማረውም ዕቃ ሁሉ እርሷን ይመርጧታል። 20ሰውም ያሳደገውን አባቱንና ሀገሩን ትቶ ሚስቱን ይከተላል። 21ስለ ሚስቱም ነፍሱን ይሰጣል፤ አባትና እናቱን፥ ሀገሩንም አያስባቸውም። 22በዚህም ሴቶች እንደሚያሸንፏችሁ ታውቃላችሁ፤ ጥራችሁና ደክማችሁም ሁሉን አምጥታችሁ ለሴቶች የምትሰጧቸው አይደላችሁምን? 23ወንድ ጦሩን ይዞ ወጥቶ ይሄዳል፤ ይሰርቃል፤ ይዘርፋልም፤ በባሕሩና በወንዙ ይጓዛል፤ 24አንበሳንም እያየ ይሄዳል፤ በጨለማም ይሄዳል። በሰረቀና በነጠቀ፥ በዘረፈም ጊዜ ሁሉን ለሚወዳት ይሰጣል። 25ወንድ ከወለዱት ከእናቱና ከአባቱ ይልቅ ሚስቱን ይወዳታል። 26በሴቶች ምክንያት ልባቸው የጠፋ፥ ስለ እነርሱም የተገዙና ባሮች የሆኑ ብዙዎች ናቸው። 27በሴቶችም ምክንያት የሞቱ፥ የተሳሳቱና የበደሉ ብዙዎች ናቸው።
28“አሁንም አታምኑኝምን? ንጉሥ በሥልጣኑ ታላቅ አይደለምን? ሕዝቡስ ሁሉ ባዩት ጊዜ እርሱን መንካት የሚፈሩ አይደለምን? 29እነሆ የንጉሡ ዕቅብት የክቡር የበርጠቁ ልጅ ኤጴሜን በንጉሡ ቀኝ ትቀመጣለች። 30የንጉሡን ዘውድ ከራሱ ላይ አውርዳ በራሷ ላይ ትደፋለች፤ ንጉሡንም በግራ እጇ በጥፊ ትመታዋለች። 31ከዚህም ሁሉ ጋራ ንጉሥ አፏን ያያል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አፉን ከፍቶ ያያታል” ይላል። ብትስቅ ይስቃል፤ ብትቈጣም ትናገር ዘንድ፥ ቍጣዋም ይበርድ ዘንድ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ይቅርታ ታደርግለት ዘንድ” ይላል። ያቈላምጣታል። 32እናንተ ሰዎች፥ እንዲህ የሚያደርጉ ሴቶች አያሸንፉምን?”
ስለ እውነት አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
33ከዚህም በኋላ ንጉሡና መኳንንቱ እርስ በርሳቸው ተያዩ፤ ከዚህም በኋላ የእውነትን ነገር ይናገር ጀመረ። 34እንዲህም አለ፥ “እናንተ ሰዎች ሆይ፥ እውነት የሚያሸንፍ አይደለምን?#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሴቶች የሚያሸንፉ አይደለምን” ይላል። ምድርስ ታላቅ ነው፤ ሰማይም ከፍ ያለ ነው፤ ፀሐይም በዙረቱ ፈጣን ነው፤ ባንዲት ቀን ሰማይን ዙሮ በቀኙ ወደ ቦታው ይመለሳልና 35እንዲህ የሚያደርግ ታላቅ አይደለምን? እውነትም ታሸንፋለች፤ ከዚህም ሁሉ ትበልጣለች። 36ዓለም ሁሉ እውነትን ይጠራታል፤ ሰማይም ይባርካታል፤ ፍጥረትም ሁሉ ለእርሷ ይንቀጠቀጣል፤ ይናወጣልም፤ ከእውነትም ጋር ዐመፃ አይገኝም። 37ወይን በደለኛ ነው፤ ንጉሥም በደለኛ ነው፤ ሴቶችም በደለኞች ናቸው፤ የሰው ልጅም በደለኛ ነው፤ ሥራቸውም ሁሉ በደል ነው፤ ይህ ሁሉ በእውነት ዘንድ የለም፤ እነዚህም ሁሉ በበደላቸው ይሞታሉ።
38“እውነት ግን ሁልጊዜ ታሸንፋለች፤ ሕይወትም ናት፤ ለዘለዓለሙም ፈጽማ ጸንታ ትኖራለች። 39በእርሷ ዘንድ ልዩነትና ለፊት ማዳላት የሉም፤ ነገር ግን እውነት በሐሰትና በክፉ ሁሉ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከሐሰትና ከክፉ ነገር ይልቅ ጽድቅን ታደርጋለች” ይላል። አትኖርም። ሰዎች ሁሉም ሥራዋን ይወድዳሉ። 40በፍርድዋም ዐመፅ የለባትም፤ እርስዋም ታሸንፋለች፥ መንግሥት፥ ገናናነትና በዓለም ውስጥ ያለ ሥልጣን ሁሉ የእርስዋ ነው፤ መንግሥት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የእውነት አምላክ” ይላል። የእርሱ የሆነ እግዚአብሔር ይመስገን” ብሎ ዝም አለ።
የዘሩባቤል ሽልማት
41ከዚህም በኋላ ሕዝቡ ሁሉ ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ፥ “እውነት ታላቅ ናት! ፈጽማም ታሸንፋለች!” አሉ። 42ንጉሡም፥ “የምትወድደውን ከተጻፈው ሁሉ አብልጠህ ለምን፤ እኔም እሰጥሃለሁ። አንተ ዐዋቂ ሆነሃልና፥ ተለይተህም ከእኔ ጋር ትቀመጣለህ፤ የእኔም ዘመድ ትሆናለህ” አለው። 43እርሱም ንጉሡን እንዲህ አለው፥ “በነገሥህ ጊዜ ኢየሩሳሌምን ትሠራት ዘንድ የተሳልኸውን ስእለት ዐስብ። 44ከኢየሩሳሌም የተወሰዱትን፥ ቂሮስ ባቢሎንን ለማጥፋት በጀመረ ጊዜ ለይቶ ያኖራቸውንና ወደዚያ ለመመለስ የተሳላቸውን ዕቃዎችን ትመልስ ዘንድ ዐስብ። 45አንተም ከለዳውያን#ግእዙ “ፋርስ” ይላል። ይሁዳን ባጠፏት ጊዜ ኤዶማውያን ያቀጠሏትን ቤተ መቅደስ ትሠራ ዘንድ ተስለሃል። 46አሁንም ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፥ የምማልድህና የምለምንህ ይህ ነው፤ ካንተም የምፈልጋት ታላቅ ነገር ይህች ናት፥ ጌታዬ ለሰማይ አምላክ የተሳልኸውን ስእለትህን ታደርግ ዘንድ እሺ በለኝ፥ ካንደበትህ የወጣውንም አድርግ።”
47ከዚህ በኋላም ንጉሡ ዳርዮስ አቅፎ ሳመው፤ እርሱንና ይሠሯት ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም የሚወጡትን ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ይሹ ዘንድ ወደ ግምጃ ቤት አዛዦችና ወደ አለቆች፥ ወደ መሳፍንቱና ወደ መኳንንቱ ሁሉ ደብዳቤዎችን ጻፈለት። 48ከእርሱም ጋር ከተማዋን ይሠሩ ዘንድ የዋንዛውን እንጨት ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያመጡ በቄሌ-ሶርያና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፌኒቄ” ን ይጨምራል። በሊባኖስ ላሉ መሳፍንት ሁሉ ደብዳቤዎችን ጻፈ።
49ኀይላቸው የሚሆኑ ባልንጀሮችንም ሁሉ ከመገዛታቸው ነጻ ያወጧቸው ዘንድ ከግዛቱ ወደ ይሁዳ ለሚወጡትም አይሁድ ሁሉ ጻፈ። የግምጃ ቤት አዛዦች፥ መሳፍንቱና መኳንንቱም ወደ በራቸው እንዳይገቡ ጻፈ። 50ባውራጃቸው ላሉትም ግብሩን ይተዉላቸው ዘንድ፥ ኤዶማውያንም አጽንተው የያዙትን ቦታቸውን ለአይሁድ ይተዉ ዘንድ ጻፈ። 51ሕንጻውም እስኪፈጸም ድረስ ለቤተ መቅደሱ ሥራ የሚሆን በየዓመቱ ሃያ መክሊት ወርቅ ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈ። 52እንደ ልማዳቸውም በሕጉ ሁልጊዜ በመሠዊያው ላይ ለሚሠዉት የዘወትር መሥዋዕት ዐሥራ ሰባት፥ በየዓመቱም ሌላ ዐሥር መክሊት ወርቅ ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈ። 53ከተማዋንም ለመሥራት ከባቢሎን ለሚመጡት ሁሉ ለእነርሱና ለልጆቻቸው አገዛዝን ይተውላቸው ዘንድ ጻፈ። 54ለሚወጡ ካህናትም ሁሉ ምግባቸውንና የሚያገለግሉበት የአገልግሎት ልብሳቸውን ጻፈላቸው። 55ለሌዋውያንም፦ የኢየሩሳሌምና የቤተ መቅደስ ሥራ እስኪፈጸም ድረስ ምግባቸውን ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈላቸው። 56ለሚያገለግሉና ከተማዋን ለሚሠሩ ሁሉ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከተማዋን ለሚጠብቁ” ይላል። ምግባቸውን ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈላቸው። 57ቂሮስ ከባቢሎን ያወጣውን ንዋየ ቅድሳቱንም ሁሉ፥ ሁሉንም ቂሮስ እንዳዘዘላቸው ያደርጉ ዘንድ፥ እርሱም እንዲሁ እንዲያደርጉና ወደ ኢየሩሳሌም እንዲልኩ አዘዛቸው።
የዘሩባቤል ጸሎት
58ከዚህም በኋላ ወጣቱ በወጣ ጊዜ በኢየሩሳሌም አንጻር ፊቱን ወደ ሰማይ አቀና፤ የሰማይንም ንጉሥ አመሰገነው። 59እንዲህም አለ፥ “ድል መንሣት ከአንተ ዘንድ ነው፤ ጥበብም ከአንተ ዘንድ ነው፤ ክብርም ለአንተ ነው፤ እኔም ያንተ ባሪያ ነኝ። 60ጥበብን የሰጠኸኝ አንተም ቡሩክ ነህ፤ የአባቶቻችን ጌታ አመሰግንሃለሁ።”
61ደብዳቤዎችንም ተቀብሎ ወደ ባቢሎን ሄደ፤ ይህንም ለወንድሞቹ ሁሉ ነገራቸው። 62ያባቶቻቸውንም አምላክ አመሰገኑ፤ ዕረፍትን ሰጥትዋቸዋልና፥ ይቅርም ብሏቸዋልና፥ 63ኢየሩሳሌምንና ስሙ የተጠራባት ቤተ መቅደስንም ይሠሩአት ዘንድ፤ ለመውጣት ፈቅዶላቸዋልና። በመሰንቆና በበገናም ደስ እያላቸው ሰባት ቀን ተቀመጡ።
Currently Selected:
መጽሐፈ ዕዝራ ካልእ 4: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ዕዝራ ካልእ 4
4
ስለ ንጉሥ አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
1ንጉሥ ያሸንፋል ያለው ሁለተኛውም ይናገር ጀመረ። 2“እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሰዎች ምድርን የሚያሸንፏት፥ ባሕርንም፥ በውስጧ ያለውንም ሁሉ የሚገዙ አይደለምን? 3ንጉሥም ለእነርሱ ጌታቸው ነው፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ነገር ግን ንጉሡ የበለጠ ኀይለኛ ነው” ይላል። ፈጽሞም ይገዛቸዋል፤ እርሱ ያዘዛቸውንም ሁሉ ያደርጋሉ። 4ባልንጀራችሁን ግደሉ ቢላቸውም ይገድላሉ ወደ ጦርነትም ሂዱ ቢላቸው ይሄዳሉ፤ ተራሮችንም ይንዳሉ፤ አጥሩንና ግንቡንም ያፈርሳሉ። 5የንጉሡንም ትእዛዝ እንቢ እንዳይሉ ይገድላሉ፤ ይገደላሉም፤ ድል ቢያደርጉም#ግእዙ “ወለእመ ሞዐ ንጉሥ” ይላል። የማረኩትን ምርኮ ሁሉ ለንጉሡ ያገባሉ።
6“ያልዘመቱና ያልተዋጉ፥ ምድርን የሚያርሱ እነርሱ ዘርተው አዝመራቸውን ባገቡ ጊዜ ግብሩን ለንጉሡ ይሰጣሉ። ለንጉሡም ግብር እንዲከፍል አንዱ ሌላውን ያስገድደዋል። 7እርሱ ግን አንድ ብቻ ነው፤ ግደሉ ቢላቸው ይገድላሉ፤ ተዉ ቢላቸውም ይተዋሉ። 8ግረፉ ቢላቸውም ይገርፋሉ፤ ገንቡ ቢላቸውም ይገነባሉ፤ አፍርሱ ቢላቸውም ያፈርሳሉ። 9ቍረጡ ቢላቸው ይቈርጣሉ፤ ትከሉ ቢላቸውም ይተክላሉ። 10ሕዝቡ ሁሉና ሠራዊቱም ላንድ ለእርሱ ይታዘዙለታል፤ ከዚህም ሁሉ ጋራ እርሱ ተቀምጦ በልቶና ጠጥቶ ይተኛል። 11ሌላውም ዙሪያውን ይጠብቃል፤ ከእነርሱም ተለይቶ ሄዶ ጉዳዩን ማድረግ የሚችል አንድም የለም፤ በማናቸውም ነገር እንቢ ይሉት ዘንድ አይችሉም። 12እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሁሉ እንዲህ የሚታዘዝለት ንጉሥ አያሸንፍምን?” ከዚህም በኋላ ዝም አለ።
ስለ ሴት አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
13ስለ ሴቶችና ስለ እውነት የተናገረው ሦስተኛውም ይናገር ጀመረ፤ እርሱም ዘሩባቤል ነው። እርሱም እንዲህ አለ፦ 14“እናንተ ሰዎችሆይ፥ ንጉሡ ታላቅ አይደለምን? ሰዎቹስ ብዙ አይደሉምን? ወይንስ ብርቱ አይደለምን? እኒህንስ የሚገዛቸውና የሚያዝዛቸው ማነው? ሴቶች አይደሉምን? 15ሴቶች ምድርንና ባሕርን የሚገዙ ንጉሡንና ሕዝቡን ሁሉ ወልደዋል። 16ከእነርሱም ተወለዱ፤ እነርሱም ከእርሱ ወይን የሚገኝበት የወይን ተክልን የሚተክሉ ሰዎችን አሳደጉ። 17እነርሱም ለሰዎች ልብስን ይሠራሉ፤ ለወንዶችም ክብርን ያደርጋሉ፤ ወንዶችም ያለ ሴት መኖር አይቻላቸውም። 18ሰዎች ምንም እንኳ ብሩንና ወርቁን፥ መልካሙንም ዕቃ ሁሉ ቢሰበስቡ፥ መልኳ ያማረና ደም ግባትዋ የተወደደ አንዲት ሴትን ባዩ ጊዜ፥ 19ያን ሁሉ ረስተው እርሷን ይመለከታሉ፤ አፏንም ያያሉ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አፋቸውን ከፍተው በትኩረት ይመለከትዋታል” ይላል። ሁሉም ያደንቋታል፤ ከወርቅና ከብር፥ ካማረውም ዕቃ ሁሉ እርሷን ይመርጧታል። 20ሰውም ያሳደገውን አባቱንና ሀገሩን ትቶ ሚስቱን ይከተላል። 21ስለ ሚስቱም ነፍሱን ይሰጣል፤ አባትና እናቱን፥ ሀገሩንም አያስባቸውም። 22በዚህም ሴቶች እንደሚያሸንፏችሁ ታውቃላችሁ፤ ጥራችሁና ደክማችሁም ሁሉን አምጥታችሁ ለሴቶች የምትሰጧቸው አይደላችሁምን? 23ወንድ ጦሩን ይዞ ወጥቶ ይሄዳል፤ ይሰርቃል፤ ይዘርፋልም፤ በባሕሩና በወንዙ ይጓዛል፤ 24አንበሳንም እያየ ይሄዳል፤ በጨለማም ይሄዳል። በሰረቀና በነጠቀ፥ በዘረፈም ጊዜ ሁሉን ለሚወዳት ይሰጣል። 25ወንድ ከወለዱት ከእናቱና ከአባቱ ይልቅ ሚስቱን ይወዳታል። 26በሴቶች ምክንያት ልባቸው የጠፋ፥ ስለ እነርሱም የተገዙና ባሮች የሆኑ ብዙዎች ናቸው። 27በሴቶችም ምክንያት የሞቱ፥ የተሳሳቱና የበደሉ ብዙዎች ናቸው።
28“አሁንም አታምኑኝምን? ንጉሥ በሥልጣኑ ታላቅ አይደለምን? ሕዝቡስ ሁሉ ባዩት ጊዜ እርሱን መንካት የሚፈሩ አይደለምን? 29እነሆ የንጉሡ ዕቅብት የክቡር የበርጠቁ ልጅ ኤጴሜን በንጉሡ ቀኝ ትቀመጣለች። 30የንጉሡን ዘውድ ከራሱ ላይ አውርዳ በራሷ ላይ ትደፋለች፤ ንጉሡንም በግራ እጇ በጥፊ ትመታዋለች። 31ከዚህም ሁሉ ጋራ ንጉሥ አፏን ያያል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አፉን ከፍቶ ያያታል” ይላል። ብትስቅ ይስቃል፤ ብትቈጣም ትናገር ዘንድ፥ ቍጣዋም ይበርድ ዘንድ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ይቅርታ ታደርግለት ዘንድ” ይላል። ያቈላምጣታል። 32እናንተ ሰዎች፥ እንዲህ የሚያደርጉ ሴቶች አያሸንፉምን?”
ስለ እውነት አሸናፊነት የቀረበ ሐተታ
33ከዚህም በኋላ ንጉሡና መኳንንቱ እርስ በርሳቸው ተያዩ፤ ከዚህም በኋላ የእውነትን ነገር ይናገር ጀመረ። 34እንዲህም አለ፥ “እናንተ ሰዎች ሆይ፥ እውነት የሚያሸንፍ አይደለምን?#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሴቶች የሚያሸንፉ አይደለምን” ይላል። ምድርስ ታላቅ ነው፤ ሰማይም ከፍ ያለ ነው፤ ፀሐይም በዙረቱ ፈጣን ነው፤ ባንዲት ቀን ሰማይን ዙሮ በቀኙ ወደ ቦታው ይመለሳልና 35እንዲህ የሚያደርግ ታላቅ አይደለምን? እውነትም ታሸንፋለች፤ ከዚህም ሁሉ ትበልጣለች። 36ዓለም ሁሉ እውነትን ይጠራታል፤ ሰማይም ይባርካታል፤ ፍጥረትም ሁሉ ለእርሷ ይንቀጠቀጣል፤ ይናወጣልም፤ ከእውነትም ጋር ዐመፃ አይገኝም። 37ወይን በደለኛ ነው፤ ንጉሥም በደለኛ ነው፤ ሴቶችም በደለኞች ናቸው፤ የሰው ልጅም በደለኛ ነው፤ ሥራቸውም ሁሉ በደል ነው፤ ይህ ሁሉ በእውነት ዘንድ የለም፤ እነዚህም ሁሉ በበደላቸው ይሞታሉ።
38“እውነት ግን ሁልጊዜ ታሸንፋለች፤ ሕይወትም ናት፤ ለዘለዓለሙም ፈጽማ ጸንታ ትኖራለች። 39በእርሷ ዘንድ ልዩነትና ለፊት ማዳላት የሉም፤ ነገር ግን እውነት በሐሰትና በክፉ ሁሉ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከሐሰትና ከክፉ ነገር ይልቅ ጽድቅን ታደርጋለች” ይላል። አትኖርም። ሰዎች ሁሉም ሥራዋን ይወድዳሉ። 40በፍርድዋም ዐመፅ የለባትም፤ እርስዋም ታሸንፋለች፥ መንግሥት፥ ገናናነትና በዓለም ውስጥ ያለ ሥልጣን ሁሉ የእርስዋ ነው፤ መንግሥት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የእውነት አምላክ” ይላል። የእርሱ የሆነ እግዚአብሔር ይመስገን” ብሎ ዝም አለ።
የዘሩባቤል ሽልማት
41ከዚህም በኋላ ሕዝቡ ሁሉ ድምፃቸውን ከፍ በማድረግ፥ “እውነት ታላቅ ናት! ፈጽማም ታሸንፋለች!” አሉ። 42ንጉሡም፥ “የምትወድደውን ከተጻፈው ሁሉ አብልጠህ ለምን፤ እኔም እሰጥሃለሁ። አንተ ዐዋቂ ሆነሃልና፥ ተለይተህም ከእኔ ጋር ትቀመጣለህ፤ የእኔም ዘመድ ትሆናለህ” አለው። 43እርሱም ንጉሡን እንዲህ አለው፥ “በነገሥህ ጊዜ ኢየሩሳሌምን ትሠራት ዘንድ የተሳልኸውን ስእለት ዐስብ። 44ከኢየሩሳሌም የተወሰዱትን፥ ቂሮስ ባቢሎንን ለማጥፋት በጀመረ ጊዜ ለይቶ ያኖራቸውንና ወደዚያ ለመመለስ የተሳላቸውን ዕቃዎችን ትመልስ ዘንድ ዐስብ። 45አንተም ከለዳውያን#ግእዙ “ፋርስ” ይላል። ይሁዳን ባጠፏት ጊዜ ኤዶማውያን ያቀጠሏትን ቤተ መቅደስ ትሠራ ዘንድ ተስለሃል። 46አሁንም ጌታዬ ንጉሥ ሆይ፥ የምማልድህና የምለምንህ ይህ ነው፤ ካንተም የምፈልጋት ታላቅ ነገር ይህች ናት፥ ጌታዬ ለሰማይ አምላክ የተሳልኸውን ስእለትህን ታደርግ ዘንድ እሺ በለኝ፥ ካንደበትህ የወጣውንም አድርግ።”
47ከዚህ በኋላም ንጉሡ ዳርዮስ አቅፎ ሳመው፤ እርሱንና ይሠሯት ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም የሚወጡትን ከእርሱ ጋር ያሉትን ሁሉ ይሹ ዘንድ ወደ ግምጃ ቤት አዛዦችና ወደ አለቆች፥ ወደ መሳፍንቱና ወደ መኳንንቱ ሁሉ ደብዳቤዎችን ጻፈለት። 48ከእርሱም ጋር ከተማዋን ይሠሩ ዘንድ የዋንዛውን እንጨት ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያመጡ በቄሌ-ሶርያና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፌኒቄ” ን ይጨምራል። በሊባኖስ ላሉ መሳፍንት ሁሉ ደብዳቤዎችን ጻፈ።
49ኀይላቸው የሚሆኑ ባልንጀሮችንም ሁሉ ከመገዛታቸው ነጻ ያወጧቸው ዘንድ ከግዛቱ ወደ ይሁዳ ለሚወጡትም አይሁድ ሁሉ ጻፈ። የግምጃ ቤት አዛዦች፥ መሳፍንቱና መኳንንቱም ወደ በራቸው እንዳይገቡ ጻፈ። 50ባውራጃቸው ላሉትም ግብሩን ይተዉላቸው ዘንድ፥ ኤዶማውያንም አጽንተው የያዙትን ቦታቸውን ለአይሁድ ይተዉ ዘንድ ጻፈ። 51ሕንጻውም እስኪፈጸም ድረስ ለቤተ መቅደሱ ሥራ የሚሆን በየዓመቱ ሃያ መክሊት ወርቅ ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈ። 52እንደ ልማዳቸውም በሕጉ ሁልጊዜ በመሠዊያው ላይ ለሚሠዉት የዘወትር መሥዋዕት ዐሥራ ሰባት፥ በየዓመቱም ሌላ ዐሥር መክሊት ወርቅ ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈ። 53ከተማዋንም ለመሥራት ከባቢሎን ለሚመጡት ሁሉ ለእነርሱና ለልጆቻቸው አገዛዝን ይተውላቸው ዘንድ ጻፈ። 54ለሚወጡ ካህናትም ሁሉ ምግባቸውንና የሚያገለግሉበት የአገልግሎት ልብሳቸውን ጻፈላቸው። 55ለሌዋውያንም፦ የኢየሩሳሌምና የቤተ መቅደስ ሥራ እስኪፈጸም ድረስ ምግባቸውን ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈላቸው። 56ለሚያገለግሉና ከተማዋን ለሚሠሩ ሁሉ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ከተማዋን ለሚጠብቁ” ይላል። ምግባቸውን ይሰጧቸው ዘንድ ጻፈላቸው። 57ቂሮስ ከባቢሎን ያወጣውን ንዋየ ቅድሳቱንም ሁሉ፥ ሁሉንም ቂሮስ እንዳዘዘላቸው ያደርጉ ዘንድ፥ እርሱም እንዲሁ እንዲያደርጉና ወደ ኢየሩሳሌም እንዲልኩ አዘዛቸው።
የዘሩባቤል ጸሎት
58ከዚህም በኋላ ወጣቱ በወጣ ጊዜ በኢየሩሳሌም አንጻር ፊቱን ወደ ሰማይ አቀና፤ የሰማይንም ንጉሥ አመሰገነው። 59እንዲህም አለ፥ “ድል መንሣት ከአንተ ዘንድ ነው፤ ጥበብም ከአንተ ዘንድ ነው፤ ክብርም ለአንተ ነው፤ እኔም ያንተ ባሪያ ነኝ። 60ጥበብን የሰጠኸኝ አንተም ቡሩክ ነህ፤ የአባቶቻችን ጌታ አመሰግንሃለሁ።”
61ደብዳቤዎችንም ተቀብሎ ወደ ባቢሎን ሄደ፤ ይህንም ለወንድሞቹ ሁሉ ነገራቸው። 62ያባቶቻቸውንም አምላክ አመሰገኑ፤ ዕረፍትን ሰጥትዋቸዋልና፥ ይቅርም ብሏቸዋልና፥ 63ኢየሩሳሌምንና ስሙ የተጠራባት ቤተ መቅደስንም ይሠሩአት ዘንድ፤ ለመውጣት ፈቅዶላቸዋልና። በመሰንቆና በበገናም ደስ እያላቸው ሰባት ቀን ተቀመጡ።