ትን​ቢተ ዳን​ኤል 10

10
ዳን​ኤል በጤ​ግ​ሮስ ወንዝ አጠ​ገብ ያየው ራእይ
1በፋ​ርስ ንጉሥ በቂ​ሮስ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥት ብል​ጣ​ሶር ለተ​ባ​ለው ለዳ​ን​ኤል ነገር ተገ​ለ​ጠ​ለት፤ ነገ​ሩም እው​ነት ነበረ፤ ታላቅ ኀይ​ልና ማስ​ተ​ዋ​ልም በራ​እዩ ውስጥ ተሰ​ጠው። 2በዚ​ያም ወራት እኔ ዳን​ኤል ሦስት ሳም​ንት ሙሉ ሳዝን ነበ​ርሁ። 3ማለ​ፊያ እን​ጀ​ራም አል​በ​ላ​ሁም፤ ሥጋና የወ​ይን ጠጅም በአፌ አል​ገ​ባም፤ ሦስ​ቱም ሳም​ንት እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ ዘይት አል​ተ​ቀ​ባ​ሁም። 4ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ወር በሃያ አራ​ተ​ኛው ቀን ጤግ​ሮስ በተ​ባ​ለው በታ​ላቁ ወንዝ አጠ​ገብ ነበ​ርሁ። 5ዐይ​ኖ​ች​ንም አነ​ሣሁ፤ እነ​ሆም በፍታ የለ​በ​ሰ​ው​ንም ጥሩም የአ​ፌ​ዝን ወርቅ በወ​ገቡ ላይ የታ​ጠ​ቀ​ውን ሰው አየሁ። 6አካ​ሉም እንደ ቢረሌ ይመ​ስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብ​ረቅ አም​ሳያ ነበረ፤ ዐይ​ኖ​ቹም እን​ደ​ሚ​ን​በ​ለ​በል ፋና፥ ክን​ዶ​ቹና እግ​ሮ​ቹም እንደ ጋለ ናስ፥ የቃ​ሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ። 7እኔም ዳን​ኤል ብቻ​ዬን ራእ​ዩን አየሁ፤ ከእኔ ጋር የነ​በሩ ሰዎች ግን ራእ​ዩን አላ​ዩም፤ ነገር ግን ታላቅ ድን​ጋጼ ወደ​ቀ​ባ​ቸው፤ ከፍ​ር​ሃ​ትም የተ​ነሣ ሸሹ። 8እኔም ብቻ​ዬን ቀረሁ፤ ይህ​ንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይ​ልም አል​ቀ​ረ​ል​ኝም፤ ክብ​ሬም ወደ ውር​ደት ተለ​ወ​ጠ​ብኝ፤ ኀይ​ልም አጣሁ። 9የቃ​ሉ​ንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃ​ሉ​ንም ድምፅ በሰ​ማሁ ጊዜ ደን​ግጬ በም​ድር ላይ በግ​ም​ባሬ ተደ​ፋሁ።
10እነ​ሆም እጅ ዳሰ​ሰ​ችኝ፤ እጄ​ንም ይዞ#“እጄ​ንም ይዞ” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። በጕ​ል​በቴ አቆ​መኝ። 11እር​ሱም፥ “እጅግ የተ​ወ​ደ​ድህ ሰው ዳን​ኤል ሆይ! እኔ ዛሬ ወደ አንተ ተል​ኬ​አ​ለ​ሁና የም​ነ​ግ​ር​ህን ቃል አስ​ተ​ውል፤ ቀጥ ብለ​ህም ቁም” አለኝ። ይህ​ንም ቃል በአ​ለኝ ጊዜ እየ​ተ​ን​ቀ​ጠ​ቀ​ጥሁ ቆምሁ። 12እር​ሱም እን​ዲህ አለኝ፥ “ዳን​ኤል ሆይ! አት​ፍራ፤ ልብህ ያስ​ተ​ውል ዘንድ፥ ሰው​ነ​ት​ህም በአ​ም​ላ​ክህ ፊት ይዋ​ረድ ዘንድ ከአ​ደ​ረ​ግ​ህ​በት ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ቀን ጀምሮ ቃልህ ተሰ​ም​ቶ​አል፤ እኔም ስለ ቃልህ መጥ​ቻ​ለሁ። 13የፋ​ርስ መን​ግ​ሥት አለቃ ግን ሃያ አንድ ቀን በፊቴ ቁሞ ነበር። እነ​ሆም ከዋ​ነ​ኞቹ አለ​ቆች አንዱ ሚካ​ኤል ሊረ​ዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋ​ርስ ንጉሥ ጋር በዚያ ተው​ሁት። 14የራ​እ​ዩም ጊዜ ገና ነውና በኋ​ለ​ኛው ዘመን ለሕ​ዝ​ብህ የሚ​ሆ​ነ​ውን አስ​ታ​ው​ቅህ ዘንድ አሁን መጥ​ቻ​ለሁ።” 15ይህ​ንም ቃል በተ​ና​ገ​ረኝ ጊዜ ፊቴን ወደ ምድር ደፋሁ፤ ዲዳም ሆንሁ። 16እነ​ሆም የሰው ልጅ የሚ​መ​ስል ከን​ፈ​ሬን ዳሰ​ሰኝ፤ ያን ጊዜም አፌን ከፍቼ ተና​ገ​ርሁ፤ በፊ​ቴም ቁሞ የነ​በ​ረ​ውን፥ “ጌታዬ ሆይ! ከራ​እዩ የተ​ነሣ ሰው​ነቴ ታወ​ከች፤ ኀይ​ልም አጣሁ። 17አቤቱ! አገ​ል​ጋ​ይህ ከጌ​ታዬ ጋር ይና​ገር ዘንድ እን​ዴት ይች​ላል? ከአ​ሁ​ንም ጀምሮ ኀይሌ አይ​ጸ​ናም፤ እስ​ት​ን​ፋ​ስም አል​ቀ​ረ​ል​ኝም” አል​ሁት።
18ደግሞ ሰው የሚ​መ​ስል ዳሰ​ሰኝ፤ አበ​ረ​ታ​ኝም። 19እር​ሱም፥ “እጅግ የተ​ወ​ደ​ድህ ሰው ሆይ! አት​ፍራ፤ ሰላም ለአ​ንተ ይሁን፤ በርታ፤ ጽና፥” አለኝ። በተ​ና​ገ​ረ​ኝም ጊዜ በረ​ታ​ሁና፥ “አበ​ር​ት​ተ​ኸ​ኛ​ልና ጌታዬ ይና​ገር” አልሁ። 20እር​ሱም እን​ዲህ አለኝ፥ “ወደ አንተ የመ​ጣ​ሁት ስለ ምን እንደ ሆነ፥ ታው​ቃ​ለ​ህን? አሁ​ንም የፋ​ር​ስን አለቃ እወ​ጋው ዘንድ እመ​ለ​ሳ​ለሁ፤ እኔም ስወጣ፥ እነሆ የግ​ሪ​ኮች አለቃ ይመ​ጣል። 21ነገር ግን በእ​ው​ነት መጽ​ሐፍ የተ​ጻ​ፈ​ውን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ በዚ​ህም ነገር ከአ​ለ​ቃ​ችሁ ከሚ​ካ​ኤል በቀር የሚ​ረ​ዳኝ ማንም የለም።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ