ትን​ቢተ ዳን​ኤል 8

8
ዳን​ኤል በራ​እይ ያያ​ቸው አውራ በግና ፍየል
1በመ​ጀ​መ​ሪያ ከተ​ገ​ለ​ጠ​ልኝ ራእይ በኋላ፥ ንጉሡ ብል​ጣ​ሶር በነ​ገሠ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ለእኔ ለዳ​ን​ኤል ራእይ ተገ​ለ​ጠ​ልኝ፤ 2በኤ​ላም አው​ራጃ በአ​ለው በሱሳ ግንብ ሳለሁ ራእይ አየሁ፤ በኡ​ባ​ልም ወንዝ አጠ​ገብ ነበ​ርሁ። 3ዐይ​ኖ​ች​ንም አቅ​ንቼ አየሁ፤ እነ​ሆም አንድ የበግ አውራ መጥቶ በኡ​ባል አጠ​ገብ ቆመ፤ ሁለት ቀን​ዶች ነበ​ሩት፤ ቀን​ዶ​ቹም ረዣ​ዥ​ሞች ነበሩ፤ አንዱ ቀንዱ ግን ከሌ​ላው ቀንዱ ይበ​ልጥ ነበር፤ ረዥ​ሙም ቀንዱ በስ​ተ​ኋላ የበ​ቀለ ነበር። 4አው​ራ​ውም በግ ወደ ምዕ​ራብ፥ ወደ ሰሜ​ንም፥ ወደ ደቡ​ብም በቅ​ንዱ ሲጐ​ሽም አየሁ፤ አራ​ዊ​ትም ሁሉ በፊቱ አይ​ቆ​ሙም ነበር፤ ከእ​ጁም የሚ​ያ​ድን አል​ነ​በ​ረም፤ እንደ ፈቃ​ዱም አደ​ረገ፤ ከፍ ከፍም አለ።
5እኔ ዳን​ኤ​ልም የባሪ ክፍል በም​ት​ሆን በሱሳ ነበ​ርሁ፤#“እኔ ዳን​ኤ​ልም የባሪ ክፍል በም​ት​ሆን በሱሳ ነበ​ርሁ” የሚ​ለው በዕብ. እና በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ስመ​ለ​ከ​ትም እነሆ ከም​ዕ​ራብ ወገን አንድ አውራ ፍየል በም​ድር ሁሉ ፊት ላይ ወጣ፤ ምድ​ር​ንም አል​ነ​ካም፤ ለፍ​የ​ሉም በዐ​ይ​ኖቹ መካ​ከል አንድ ታላቅ ቀንድ ነበ​ረው። 6ሁለ​ትም ቀንድ ወደ አለው፥ በኡ​ባል ወን​ዝም ፊት ቆሞ ወደ አየ​ሁት አውራ በግ መጣ፤ በኀ​ይ​ሉም ቍጣ ፈጥኖ ወደ እርሱ ሮጠ። 7ወደ አው​ራ​ውም በግ ቀርቦ አየ​ሁት፤ እር​ሱም ዘልሎ ወጣ​በት፤ አው​ራ​ው​ንም በግ መታ፤ ሁለ​ቱ​ንም ቀን​ዶች ሰበረ፤ አው​ራ​ውም በግ በፊቱ ሊቆም ኀይል አል​ነ​በ​ረ​ውም፤ እር​ሱም በም​ድር ላይ ጥሎ ረገ​ጠው፤ አው​ራ​ው​ንም በግ ከእጁ ያድን ዘንድ የሚ​ችል አል​ነ​በ​ረም። 8አው​ራ​ውም ፍየል ራሱን እጅግ ታላቅ አደ​ረገ፤ በበ​ረ​ታም ጊዜ ታላቁ ቀንዱ ተሰ​በረ፤ ወደ አራ​ቱም የሰ​ማይ ነፋ​ሳት የሚ​መ​ለ​ከቱ አራት ቀን​ዶች ከበ​ታቹ ወጡ።
9ከእ​ነ​ር​ሱም ከአ​ን​ደ​ኛው አንድ ጠን​ካራ ቀንድ ወጣ፤ ወደ ደቡ​ብም፥ ወደ ምሥ​ራ​ቅም፥ ወደ መል​ካ​ሚ​ቱም ምድር#“ወደ መል​ካ​ሚቱ ምድር” የሚ​ለው በዕብ. ብቻ። እጅግ ከፍ አለ። 10እስከ ሰማ​ይም ሠራ​ዊት ድረስ ከፍ አለ፤ ከሰ​ማይ ሠራ​ዊ​ትና ከሰ​ማይ ከዋ​ክ​ብ​ትም የተ​ወ​ሰ​ኑ​ትን ወደ ምድር ጣለ፥ ረገ​ጣ​ቸ​ውም። 11እስከ ሠራ​ዊ​ትም አለቃ ድረስ ምር​ኮን አዳነ፤#ዕብ. “ራሱን ታላቅ አደ​ረገ” ይላል። ከእ​ር​ሱም የተ​ነሣ የዘ​ወ​ትሩ መሥ​ዋ​ዕት ተሻረ፤ የመ​ቅ​ደ​ሱም ስፍራ ፈረሰ። 12የኀ​ጢ​አ​ትም መሥ​ዋ​ዕት ከዘ​ወ​ትሩ መሥ​ዋ​ዕት ጋር ተሰጠ፤ እው​ነ​ትም ወደ ምድር ተጣ​ለች፤ አደ​ረ​ገም፤ ተከ​ና​ወ​ነም። 13ከቅ​ዱ​ሳ​ኑም አንዱ ሲና​ገር ሰማሁ፤ ለተ​ና​ገ​ረው ለቅ​ዱ​ሱም ሁለ​ተ​ኛው ቅዱስ “ስለ ዘወ​ትሩ መሥ​ዋ​ዕት፥ መቅ​ደ​ሱና ሠራ​ዊ​ቱም ይረ​ገጡ ዘንድ ስለ​ሚ​ሰ​ጥና ስለ​ሚ​ያ​ጠፋ ኀጢ​አት የሆ​ነው ይህ ራእይ እስከ መቼ ይቈ​ያል?” አለው። 14እር​ሱም፥ “እስከ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ማታና ጥዋት ድረስ ነው፤ ከዚ​ያም በኋላ መቅ​ደሱ ይነ​ጻል” አለኝ።
መል​አኩ ቅዱስ ገብ​ር​ኤል ራእ​ዩን ለዳ​ን​ኤል እንደ ተረ​ጐ​መ​ለት
15እኔም ዳን​ኤል ራእ​ዩን በአ​የሁ ጊዜ ልረ​ዳው ፈለ​ግሁ፤ እነ​ሆም የሰው አም​ሳል በፊቴ ቆሞ ነበር። 16በኡ​ባ​ልም ወንዝ መካ​ከል የሰው ድምፅ ሰማሁ፤ ጠር​ቶም “ገብ​ር​ኤል ሆይ! ራእ​ዩን ለዚህ ሰው ግለ​ጥ​ለት” አለ። 17እኔም ወደ ቆም​ሁ​በት ቀረበ፤ በመ​ጣም ጊዜ ፈርቼ በግ​ን​ባሬ ተደ​ፋሁ፤ እር​ሱም፥ “የሰው ልጅ ሆይ! ራእዩ ለፍ​ጻሜ ዘመን እንደ ሆነ አስ​ተ​ውል” አለኝ። 18ሲና​ገ​ረ​ኝም ደን​ግጬ በም​ድር ላይ በግ​ን​ባሬ ተደ​ፋሁ፤ እር​ሱም ዳሰ​ሰኝ፤ አን​ሥ​ቶም በእ​ግሬ አቆ​መኝ። 19እን​ዲ​ህም አለኝ- “እነሆ በመ​ቅ​ሠ​ፍቱ በመ​ጨ​ረሻ ዘመን የሚ​ሆ​ነ​ውን አስ​ታ​ው​ቅ​ሃ​ለሁ፤ ይህ ገና ለፍ​ጻሜ ዘመን ነውና። 20ያየ​ኸው፥ ቀን​ዶች ያሉት አውራ በግ የሜ​ዶ​ንና የፋ​ርስ ንጉሥ ነው።#ዕብ. “በአ​የ​ኸው በአ​ው​ራው በግ ላይ የነ​በሩ ሁለቱ ቀን​ዶች እነ​ርሱ የሜ​ዶ​ንና የፋ​ርስ ነገ​ሥ​ታት ናቸው” ይላል። 21አው​ራ​ውም ፍየል የግ​ሪ​ኮች ንጉሥ ነው፤ በዐ​ይ​ኖ​ቹም መካ​ከል ያለው ታላቁ ቀንድ መጀ​መ​ሪ​ያው ንጉሥ ነው። 22እር​ሱም በቆ​መ​በት በተ​ሰ​በረ ጊዜ በእ​ርሱ ፋንታ አራቱ እንደ ተነሡ፤ እን​ዲሁ ከወ​ገኑ አራት መን​ግ​ሥ​ታት ይነ​ሣሉ፤ ነገር ግን በኀ​ይል አይ​ተ​ካ​ከ​ሉ​ትም። 23በመ​ን​ግ​ሥ​ታ​ቸ​ውም መጨ​ረሻ ኀጢ​አ​ታ​ቸው በተ​ሞ​ላች ጊዜ፥ እን​ቆ​ቅ​ል​ሽን የሚ​ያ​ስ​ተ​ውል፥ ፊቱ ጨካኝ የሆነ ንጉሥ ይነ​ሣል። 24ኀይ​ሉም ይበ​ረ​ታል፤ በተ​አ​ም​ርም ያጠ​ፋል፤ ያደ​ር​ግ​ማል፤ ያከ​ና​ወ​ን​ማል፤ ኀያ​ላ​ን​ንና ቅዱ​ሳ​ንን ሕዝብ ያጠ​ፋል። 25ያን​ገ​ቱን ቀን​በር ያቀ​ናል። ተን​ኰል በእጁ አለ፤ በል​ቡም ይታ​በ​ያል፤ በሽ​ን​ገ​ላም ብዙ​ዎ​ችን ያጠ​ፋል፤ በአ​ለ​ቆ​ቹም አለቃ ላይ ይቆ​ማል፤ ያለ እጅም ይሰ​ብ​ራል። 26የተ​ነ​ገ​ረ​ውም የማ​ታ​ውና የጥ​ዋቱ ራእይ እው​ነ​ተኛ ነው፤ ነገር ግን ከብዙ ዘመን በኋላ ስለ​ሚ​ሆን ራእ​ዩን ዝጋ።” 27እኔም ዳን​ኤል ተኛሁ፤ አያ​ሌም ቀን ታመ​ምሁ፤ ከዚ​ያም በኋላ ተነ​ሥቼ የን​ጉ​ሡን ሥራ እሠራ ነበር፤ ስለ ራእ​ዩም አደ​ንቅ ነበር፤ የሚ​ያ​ስ​ተ​ው​ለው ግን አል​ነ​በ​ረም።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ