ትን​ቢተ ሕዝ​ቅ​ኤል 4

4
ሕዝ​ቅ​ኤል የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን በጠ​ላት መከ​በብ እንደ አስ​ረዳ
1“አን​ተም የሰው ልጅ ሆይ! ጡብን ወስ​ደህ በፊ​ትህ አኑ​ራት፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ከተማ ሥዕል ሣል​ባት፤ 2በው​ስ​ጧም የሚ​ዋ​ጉ​በት ግን​ብን ሥራ፤ በሠ​ራ​ዊ​ትም ክበ​ባት፤ በዙ​ሪ​ያ​ዋም ጦር አስ​ፍር፤ የሚ​ዋጋ ጦር​ንም ወደ አደ​ባ​ባ​ይዋ ላክ። 3የብ​ረት ምጣ​ድም ወስ​ደህ በአ​ን​ተና በከ​ተ​ማ​ዪቱ መካ​ከል ለብ​ረት ቅጥር አድ​ር​ገው፤ ፊት​ህ​ንም ወደ እር​ስዋ አቅና፤ የተ​ከ​በ​በ​ችም ትሆ​ና​ለች፤ አን​ተም ትከ​ብ​ባ​ታ​ለህ። ይህም ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ምል​ክት ይሆ​ናል።
4“አን​ተም በግራ ጎንህ ተኛ፤ በም​ት​ተ​ኛ​በ​ትም ቀን ቍጥር#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አንድ መቶ አምሳ” ይላል። የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ቤት ኀጢ​አት አኑ​ር​ባት፤ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም ትሸ​ከ​ማ​ለህ። 5እኔም የኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ዓመ​ታት ለአ​ንተ የቀን ቍጥር እን​ዲ​ሆ​ን​ልህ ሦስት መቶ ዘጠና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አንድ መቶ ዘጠና” ይላል። ቀን ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ቤት ኃጢ​አት ትሸ​ከ​ማ​ለህ፤ 6እነ​ዚ​ህ​ንም በፈ​ጸ​ምህ ጊዜ በቀኝ ጎንህ ትተ​ኛ​ለህ፤ የይ​ሁ​ዳ​ንም ቤት ኀጢ​አት አርባ ቀን ትሸ​ከ​ማ​ለህ፤ አን​ዱን ቀን አንድ ዓመት አደ​ረ​ግ​ሁ​ልህ። 7ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ከበባ ፊት​ህን ታቀ​ና​ለህ፤ ክን​ድ​ህ​ንም ታጸ​ና​ለህ፤ በእ​ር​ሷም ትን​ቢ​ትን ትና​ገ​ራ​ለህ። 8እነ​ሆም ገመድ አደ​ር​ግ​ብ​ሃ​ለሁ፤ የም​ት​ከ​በ​ብ​በ​ት​ንም ወራት እስ​ክ​ት​ፈ​ጽም ድረስ ከጎን ወደ ጎንህ አት​ገ​ላ​በ​ጥም።
9“አን​ተም ስን​ዴ​ንና ገብ​ስን፥ አተ​ር​ንና ባቄ​ላን፥ ምስ​ር​ንና አጃን ወደ አንተ ውሰድ፤ በአ​ንድ ዕቃም ውስጥ አድ​ር​ገህ እን​ጀራ ጋግር፤ በጎ​ንህ እንደ ተኛ​ህ​ባት ቀን ቍጥር ሦስት መቶ ዘጠና#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አንድ መቶ ዘጠና” ይላል። ቀን ትበ​ላ​ዋ​ለህ። 10የም​ት​በ​ላ​ውም በሚ​ዛን በየ​ቀኑ ሃያ ሃያ ሰቅል ይሁን፤ በየ​ጊ​ዜው ትበ​ላ​ዋ​ለህ። 11ውኃ​ው​ንም በልክ የኢን መስ​ፈ​ሪያ ከስ​ድ​ስት እጅ አንድ እጅ ትጠ​ጣ​ለህ፤ በየ​ጊ​ዜው ትጠ​ጣ​ዋ​ለህ። 12የገ​ብስ እን​ጎ​ቻ​ንም ትበ​ላ​ለህ፤ በሰው ኵስም ታበ​ስ​ለ​ዋ​ለህ፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም ታዳ​ፍ​ነ​ዋ​ለህ።”
13እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “እን​ዲሁ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እነ​ር​ሱን በም​በ​ት​ን​ባ​ቸው በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ንጹሕ ያል​ሆነ እን​ጀ​ራ​ቸ​ውን ይበ​ላሉ” አለ። 14እኔም፥ “የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ! ይህ አግ​ባብ አይ​ደ​ለም፤ እነሆ ሰው​ነቴ አል​ረ​ከ​ሰ​ችም፤ ከታ​ና​ሽ​ነቴ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ጥን​ብና አውሬ የሰ​በ​ረ​ውን ከቶ አል​በ​ላ​ሁም፤ ርኵ​ስም ሥጋ በአፌ ውስጥ አል​ገ​ባም” አልሁ። 15እር​ሱም፥ “እነሆ በሰው ኵስ ፋንታ የከ​ብት ኩበት ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ በእ​ር​ሱም እን​ጀ​ራ​ህን ትጋ​ግ​ራ​ለህ” አለኝ። 16ደግ​ሞም እን​ዲህ አለኝ፥ “የሰው ልጅ ሆይ! የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን እን​ጀራ በትር እሰ​ብ​ራ​ለሁ፤ በች​ግር እያሉ እን​ጀ​ራን በሚ​ዛን ይበ​ላሉ፥ እየ​ደ​ነ​ገ​ጡም ውኃን በልክ ይጠ​ጣሉ፤ 17ይህም እን​ጀ​ራ​ንና ውኃን እን​ዲ​ያጡ፥ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም እን​ዲ​ገ​ዳ​ደሉ፥ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ውም እን​ዲ​ጠፉ ነው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ