መዝ​ሙረ ዳዊት 118

118
አሌፍ።
1በመ​ን​ገ​ዳ​ቸው ንጹ​ሓን የሆኑ፥
በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕግ የሚ​ሄዱ ብፁ​ዓን ናቸው።
2ምስ​ክ​ሩን የሚ​ፈ​ልጉ፥
በፍ​ጹም ልብ የሚ​ሹት ብፁ​ዓን ናቸው፤
3ዐመ​ፃን የሚ​ያ​ደ​ርጉ ግን በመ​ን​ገዱ አይ​ሄ​ዱም።
4ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን እጅግ ይጠ​ብቁ ዘንድ አንተ አዘ​ዝህ።
5ሥር​ዐ​ት​ህን እጠ​ብቅ ዘንድ
የሚ​ቀ​ናስ ከሆነ መን​ገዴ ይቅና።
6ትእ​ዛ​ዝ​ህን ሁሉ ስመ​ለ​ከት
በዚ​ያን ጊዜ አላ​ፍ​ርም።
7አቤቱ፥ የጽ​ድ​ቅ​ህን ፍርድ ስማር
በቅን ልብ አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ።
8ሥር​ዐ​ት​ህ​ንም እጠ​ብ​ቃ​ለሁ፤
ለዘ​ለ​ዓ​ለም አት​ጣ​ለኝ።
ቤት።
9ጐል​ማሳ መን​ገ​ዱን በምን ያቀ​ናል?
ቃል​ህን በመ​ጠ​በቅ ነው።
10በፍ​ጹም ልቤ ፈለ​ግ​ሁህ፥
ከት​እ​ዛ​ዝህ አታ​ር​ቀኝ።
11አን​ተን እን​ዳ​ል​በ​ድል፥
ቃል​ህን በልቤ ሰወ​ርሁ።
12አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ፤
ሥር​ዐ​ት​ህ​ንም አስ​ተ​ም​ረኝ።
13የአ​ፍ​ህን ፍርድ ሁሉ በከ​ን​ፈሬ ነገ​ርሁ።
14እንደ ብል​ጥ​ግና ሁሉ
በም​ስ​ክ​ርህ መን​ገድ ደስ አለኝ።
15ትእ​ዛ​ዝ​ህን አሰ​ላ​ሰ​ልሁ፥
መን​ገ​ድ​ህ​ንም እፈ​ል​ጋ​ለሁ።
16ትእ​ዛ​ዞ​ች​ህን አነ​ብ​ባ​ለሁ፤
ቃል​ህ​ንም አል​ረ​ሳም።
ጋሜል።
17ሕያው እን​ድ​ሆን ቃል​ህ​ንም እን​ድ​ጠ​ብቅ
ለባ​ሪ​ያህ ስጠው።
18ዓይ​ኖ​ችን ክፈት፥
ከሕ​ግ​ህም ድንቅ ነገ​ርን አያ​ለሁ።
19እኔ በም​ድር ስደ​ተኛ ነኝ፤
ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን ከእኔ አት​ሰ​ውር።
20ነፍሴ ሁል​ጊዜ ፍር​ድ​ህን እጅግ ናፈ​ቀች።
ትዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችን ገሠ​ጽ​ኻ​ቸው፥
21ከት​እ​ዛ​ዛ​ትህ የሚ​ርቁ ርጉ​ማን ናቸው።
22ትእ​ዛ​ዝ​ህን#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ምስ​ክ​ር​ህን” ይላል። ፈል​ጌ​አ​ለ​ሁና
ስድ​ብ​ንና ነው​ርን ከእኔ አርቅ።
23አለ​ቆች ደግሞ ተቀ​ም​ጠው እኔን አሙኝ፤
ባሪ​ያህ ግን ፍር​ድ​ህን ያሰ​ላ​ስል ነበር።
24ምስ​ክ​ር​ህም ትም​ህ​ርቴ ነው፥
ሥር​ዐ​ት​ህም መካሬ ነው።
ዳሌጥ።
25ሰው​ነቴ ወደ ምድር ተጣ​በ​ቀች፤
እንደ ቃልህ ሕያው አድ​ር​ገኝ።
26መን​ገ​ድ​ህ​ንና ምስ​ክ​ር​ህን ነገ​ርሁ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሰማ​ኸ​ኝም” የሚል ይጨ​ም​ራል።
ፍር​ድ​ህን አስ​ተ​ም​ረኝ።
27የእ​ው​ነ​ት​ህን መን​ገድ እን​ዳ​ስ​ተ​ውል አድ​ር​ገኝ፥
ተአ​ም​ራ​ት​ህ​ንም አሰ​ላ​ስ​ላ​ለሁ።
28ከኀ​ዘን የተ​ነሣ ሰው​ነቴ አን​ቀ​ላ​ፋች፤
በቃ​ልህ አጠ​ን​ክ​ረኝ።
29የዐ​መ​ፃን መን​ገድ ከእኔ አርቅ፥
በሕ​ግ​ህም ይቅር በለኝ፤
30የእ​ው​ነ​ት​ህን መን​ገድ መረ​ጥሁ፥
ፍር​ድ​ህ​ንም አል​ረ​ሳ​ሁም።
31አቤቱ፥ ምስ​ክ​ር​ህን ተከ​ተ​ልሁ፥ አታ​ሳ​ፍ​ረኝ።
32ልቤን ባሰ​ፋ​ኸው ጊዜ፥
በት​እ​ዛ​ዝህ መን​ገድ ሮጥሁ።
ሄ።
33አቤቱ፥ የእ​ው​ነ​ት​ህን መን​ገድ አስ​ተ​ም​ረኝ፥
ሁል​ጊ​ዜም እፈ​ል​ጋ​ታ​ለሁ።
34እን​ዳ​ስ​ተ​ውል አድ​ር​ገኝ፥ ሕግ​ህ​ንም እፈ​ል​ጋ​ለሁ፤
በፍ​ጹም ልቤም እጠ​ብ​ቀ​ዋ​ለሁ።
35እር​ስ​ዋን ወድ​ጃ​ለ​ሁና
የት​እ​ዛ​ዝ​ህን መን​ገድ ምራኝ።
36ልቤን ወደ ምስ​ክ​ርህ መልስ፥
ወደ ቅሚ​ያም አይ​ሁን።
37ከንቱ ነገ​ርን እን​ዳ​ያዩ ዐይ​ኖ​ቼን መልስ፤
በመ​ን​ገ​ድ​ህም ሕያው አድ​ር​ገኝ።
38እን​ዲ​ፈ​ራህ#“እን​ዲ​ፈ​ራህ” የሚ​ለው በግ​እዝ የለም። ለባ​ሪ​ያህ በቃ​ልህ የተ​ና​ገ​ር​ኸ​ውን አጽና።
39ፍር​ድህ መል​ካም ነውና
የተ​ጠ​ራ​ጠ​ር​ሁ​ትን ስድብ ከእኔ አርቅ።
40እነሆ፥ ትእ​ዛ​ዝ​ህን ናፈ​ቅሁ፥
በጽ​ድ​ቅ​ህም ሕያው አድ​ር​ገኝ።
ዋው።
41አቤቱ፥ ምሕ​ረ​ትህ ይም​ጣ​ልኝ፥
አቤቱ፥ ማዳ​ንህ እንደ ቃልህ ነው።
42በቃ​ልህ ታም​ኛ​ለ​ሁና
ለሚ​ሰ​ድ​ቡኝ በነ​ገር እመ​ል​ስ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ።
43በፍ​ር​ድ​ህም ታም​ኛ​ለ​ሁና
የእ​ው​ነ​ትን ቃል ከአፌ ፈጽ​መህ አታ​ርቅ።
44ለዘ​ለ​ዓ​ለም ዓለም
ሁል​ጊዜ ሕግ​ህን እጠ​ብ​ቃ​ለሁ።
45ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህ​ንም ፈል​ጌ​አ​ለ​ሁና
አስ​ፍቼ እሄ​ዳ​ለሁ።
46በነ​ገ​ሥ​ታት ፊት ምስ​ክ​ር​ህን እና​ገ​ራ​ለሁ፥ አላ​ፍ​ር​ምም፤
47እጅ​ግም የወ​ደ​ድ​ኋ​ቸ​ውን ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን እና​ገ​ራ​ለሁ።
48እጆ​ቼ​ንም ወደ ወደ​ድ​ኋ​ቸው ወደ ትእ​ዛ​ዛ​ትህ አነ​ሣ​ለሁ፤
ፍር​ድ​ህ​ንም አሰ​ላ​ስ​ላ​ለሁ።
ዛይ።
49ለባ​ሪ​ያህ ተስፋ ያስ​ደ​ረ​ግ​ኸ​ውን ቃል​ህን አስብ።
50ቃልህ ሕያው አድ​ር​ጎ​ኛ​ልና።
ይህች በመ​ከ​ራዬ ደስ አሰ​ኘ​ችኝ።
51ትዕ​ቢ​ተ​ኞች እጅግ ዐመፁ፤
እኔ ግን ከሕ​ግህ አል​ራ​ቅ​ሁም።
52ከጥ​ንት የነ​በ​ረ​ውን ፍር​ድ​ህን ዐሰ​ብሁ፥
አቤቱ፥ደስ አለኝ።
53ሕግ​ህን ከተዉ ኃጥ​ኣን የተ​ነሣ ኀዘን ያዘኝ።
54በእ​ን​ግ​ድ​ነቴ ሀገር ፍር​ድህ መዝ​ሙር ሆነኝ።
55አቤቱ፥ በሌ​ሊት ስም​ህን ዐሰ​ብሁ፥
ሕግ​ህ​ንም ጠበ​ቅሁ።
56ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህ​ንም ፈል​ጌ​አ​ለ​ሁና ይህች ሆነ​ች​ልኝ።
ሔት።
57እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክፍሌ ነው፤
ሕግ​ህን ይጠ​ብቁ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እጠ​ብ​ቃ​ለሁ” ይላል። አልሁ።
58አቤቱ በፍ​ጹም ልቤ ወደ ፊትህ ለመ​ንሁ፤
እንደ ቃልህ ይቅር በለኝ።
59ስለ መን​ገ​ዶ​ችህ ዐሰ​ብሁ፥
እግ​ሬ​ንም ወደ ምስ​ክ​ርህ መለ​ስሁ።
60ትእ​ዛ​ዝ​ህን ለመ​ጠ​በቅ ጨከ​ንሁ፥ አል​ተ​ጠ​ራ​ጠ​ር​ሁ​ምም።
61የኃ​ጥ​ኣን ገመ​ዶች ተተ​በ​ተ​ቡ​ብኝ፤
ሕግ​ህን ግን አል​ረ​ሳ​ሁም።
62ስለ ጽድ​ቅህ ፍርድ፥ አመ​ሰ​ግ​ንህ ዘንድ
በእ​ኩለ ሌሊት እነ​ሣ​ለሁ።
63እኔ ለሚ​ፈ​ሩህ ሁሉ፥
ትእ​ዛ​ዝ​ህ​ንም ለሚ​ጠ​ብቁ ባል​ን​ጀራ ነኝ።
64አቤቱ፥ ይቅ​ር​ታህ በም​ድር ሁሉ ሞላች፤
ሥር​ዐ​ት​ህ​ንም አስ​ተ​ም​ረኝ።
ጤት።
65አቤቱ፥ እንደ ቃልህ
ለባ​ሪ​ያህ መል​ካም አደ​ረ​ግህ።
66በት​እ​ዛ​ዛ​ትህ ታም​ኛ​ለ​ሁና
መል​ካም ምክ​ር​ንና ጥበ​ብን አስ​ተ​ም​ረኝ።
67እኔ ሳል​ጨ​ነቅ ተጸ​ጸ​ትሁ፤#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “በደ​ልሁ” ይላል።
ስለ​ዚ​ህም ቃል​ህን ጠበ​ቅሁ።
68አቤቱ፥ አንተ ቸር ነህ፥
በቸ​ር​ነ​ት​ህም ፍር​ድ​ህን አስ​ተ​ም​ረኝ።
69የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ዐመፃ በላዬ በዛ፤
እኔ ግን በፍ​ጹም ልቤ ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን እፈ​ል​ጋ​ለሁ።
70ልባ​ቸው እንደ ወተት ረጋ፤
እኔ ግን ሕግ​ህን አነ​ብ​ባ​ለሁ
71ፍር​ድ​ህን አውቅ ዘንድ
ያስ​ጨ​ነ​ቅ​ኸኝ መል​ካም ሆነ​ልኝ።
72ከአ​እ​ላ​ፋት ወር​ቅና ብር ይልቅ።
የአ​ፍህ ሕግ ይሻ​ለ​ኛል።
ዮድ።
73እጆ​ችህ ሠሩኝ፥ አበ​ጃ​ጁ​ኝም፤
እን​ዳ​ስ​ተ​ውል አድ​ር​ገኝ፥ ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህ​ንም እማ​ራ​ለሁ።
74በቃ​ልህ ታም​ኛ​ለ​ሁና
የሚ​ፈ​ሩህ እኔን አይ​ተው ደስ ይላ​ቸ​ዋል።
75አቤቱ፥ ፍር​ድህ ጽድቅ እንደ ሆነች፥
በሚ​ገ​ባም እን​ዳ​ስ​ጨ​ነ​ቅ​ኸኝ ዐወ​ቅሁ።
76ምሕ​ረ​ትህ ለደ​ስ​ታዬ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ለመ​ጽ​ና​ናቴ” ይላል። ይሁ​ነኝ፥
እንደ ቃል​ህም ለባ​ሪ​ያህ ይሁ​ነው።
77ሕግህ ትም​ህ​ርቴ ነውና
ቸር​ነ​ትህ ይም​ጣ​ልኝ፥ በሕ​ይ​ወ​ትም ልኑር።
78ትዕ​ቢ​ተ​ኞች ዐመ​ፃን መክ​ረ​ው​ብ​ኛ​ልና ይፈሩ፤
እኔ ግን ትእ​ዛ​ዝ​ህን አሰ​ላ​ስ​ላ​ለሁ።
79የሚ​ፈ​ሩ​ህና ምስ​ክ​ሮ​ች​ህን የሚ​ያ​ውቁ ወደ እኔ ይመ​ለሱ።
80እን​ዳ​ላ​ፍር ልቤ በፍ​ር​ድህ ንጹሕ ይሁን።
ካፍ።
81ነፍሴ ወደ ማዳ​ንህ አለ​ፈች፤
በቃ​ል​ህም ታመ​ንሁ።
82መቼ ታጽ​ና​ና​ኛ​ለህ እያ​ልሁ
ዐይ​ኖቼ ትድ​ግ​ና​ህን በመ​ጠ​በቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ስለ ቃልህ” ይላል። ፈዘዙ።
83በው​ርጭ እን​ዳለ ረዋት ሆኛ​ለ​ሁና፤
ፍር​ድ​ህን ግን አል​ረ​ሳ​ሁም።
84የባ​ሪ​ያህ ዘመ​ኖች ምን ያህል ናቸው?
በሚ​ያ​ሳ​ድ​ዱ​ኝስ ላይ መቼ ትፈ​ር​ድ​ል​ኛ​ለህ?
85ኃጥ​ኣን ዋዛ-ፈዛ​ዛን ነገ​ሩኝ፥
አቤቱ፥ እንደ ሕግህ ግን አይ​ደ​ለም።
86ትእ​ዛ​ዝ​ትህ ሁሉ እው​ነት ናቸው፤
በዐ​መፃ አሳ​ድ​ደ​ው​ኛል፤ ርዳኝ።
87ከም​ድር ሊያ​ጠ​ፉኝ ጥቂት ቀር​ቶ​አ​ቸው ነበር፤
እኔ ግን ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን አል​ተ​ው​ሁም።
88እንደ ምሕ​ረ​ትህ ሕያው አድ​ር​ገኝ፤
የአ​ፍ​ህ​ንም ምስ​ክር እጠ​ብ​ቃ​ለሁ።
ላሜድ።
89አቤቱ፥ ቃልህ በሰ​ማይ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይኖ​ራል።
90እው​ነ​ትህ ለልጅ ልጅ ናት፤
ምድ​ርን መሠ​ረ​ት​ሃት፥ እር​ስ​ዋም ትኖ​ራ​ለች።
91ሁሉን ገዝ​ተ​ሃ​ልና
ቀኑ በት​እ​ዛ​ዝህ ይኖ​ራል።
92ሕግህ ትም​ህ​ርቴ ባይ​ሆን፥
ቀድሞ በጕ​ስ​ቍ​ል​ናዬ በጠ​ፋሁ ነበር።
93በእ​ርሱ ሕያው አድ​ር​ገ​ኸ​ኛ​ልና
ፍር​ድ​ህን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አል​ረ​ሳም።
94እኔ የአ​ንተ ነኝ፥ ፍር​ድ​ህን ፈል​ጌ​አ​ለ​ሁና አድ​ነኝ።
95ኃጥ​ኣን ያጠ​ፉኝ ዘንድ ጠበ​ቁኝ፤
ምስ​ክ​ር​ህን አስ​ተ​ው​ያ​ለ​ሁና።
96የሥ​ራ​ውን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ፤
ትእ​ዛ​ዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው።
ሜም።
97አቤቱ፥ ሕግ​ህን እን​ደ​ምን እጅግ ወደ​ድሁ!
ቀኑን ሁሉ እርሱ ትም​ህ​ርቴ ነው።
98ለዘ​ለ​ዓ​ለም ለእኔ ነውና
ትእ​ዛ​ዝህ ከጠ​ላ​ቶቼ ይልቅ አስ​ተ​ዋይ አደ​ረ​ገኝ።
99ትእ​ዛ​ዝህ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ምስ​ክ​ርህ” ይላል። ትም​ህ​ርቴ ነውና
ካስ​ተ​ማ​ሩኝ ሁሉ ይልቅ አስ​ተ​ዋ​ልሁ።
100ትእ​ዛ​ዝ​ህን ፈል​ጌ​አ​ለ​ሁና
ከሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎች ይልቅ አስ​ተ​ዋ​ልሁ።
101ቃል​ህን እጠ​ብቅ ዘንድ
ከክፉ መን​ገድ ሁሉ እግ​ሬን ከለ​ከ​ልሁ።
102አንተ አስ​ተ​ም​ረ​ኸ​ኛ​ልና ከፍ​ር​ድህ አል​ራ​ቅ​ሁም።
103ቃልህ ለጕ​ሮ​ሮዬ ጣፋጭ ነው፤
ከማ​ርና ከወ​ለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈ​ጠኝ።
104ከት​እ​ዛ​ዝህ የተ​ነሣ አስ​ተ​ዋ​ልሁ፤
ስለ​ዚህ የዐ​መ​ፃን መን​ገድ ጠላሁ።
ኖን።
105ሕግህ ለእ​ግሬ መብ​ራት፥
ለመ​ን​ገ​ዴም ብር​ሃን ነው።
106የጽ​ድ​ቅ​ህን ፍርድ እጠ​ብቅ ዘንድ ማልሁ፥ አጸ​ና​ሁም።
107እጅግ መከራ ተቀ​በ​ልሁ፥
አቤቱ፥ እንደ ቃልህ ሕያው አድ​ር​ገኝ።
108አቤቱ፥ ከአፌ የሚ​ወ​ጣ​ውን ቃል ውደድ፥
ፍር​ድ​ህ​ንም አስ​ተ​ም​ረኝ።
109ነፍሴ ሁል​ጊዜ በእ​ጅህ ውስጥ ናት፤
ሕግ​ህን ግን አል​ረ​ሳ​ሁም።
110ኃጥ​ኣን ወጥ​መ​ድን ዘረ​ጉ​ብኝ፤
ከት​እ​ዛ​ዝህ ግን አል​ሳ​ት​ሁም።
111የልቤ ደስታ ነውና
ምስ​ክ​ር​ህን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ወረ​ስሁ።
112ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያለ ነቀፋ
ትእ​ዛ​ዝ​ህን አደ​ርግ ዘንድ ልቤን መለ​ስሁ።
ሳም​ኬት።
113ዐመ​ፀ​ኞ​ችን ጠላሁ፥ ሕግ​ህን ግን ወደ​ድሁ።
114አንተ ረዳ​ቴና መጠ​ጊ​ያዬ ነህ፥
በቃ​ል​ህም ተማ​መ​ንሁ።
115እና​ንተ ዐመ​ፀ​ኞች፥ ከእኔ ራቁ፥
የአ​ም​ላ​ኬ​ንም ትእ​ዛዝ ልፈ​ልግ።
116እንደ ቃልህ ተቀ​በ​ለኝ፥ ሕያ​ውም እሆ​ና​ለሁ፤
ከተ​ስ​ፋ​ዬም አታ​ሳ​ፍ​ረኝ።
117ርዳ​ኝም፥ አድ​ነ​ኝም፥
ሁል​ጊ​ዜም ፍር​ድ​ህን አነ​ብ​ባ​ለሁ።
118ምኞ​ታ​ቸው ዐመፃ ነውና
ከሥ​ር​ዐ​ትህ የሚ​ር​ቁ​ትን ሁሉ አጐ​ሳ​ቈ​ል​ሃ​ቸው።
119የም​ድር ኃጥ​ኣን ሁሉ ወን​ጀ​ለ​ኞች#ዕብ. “እንደ ርኵ​ሰት አጠ​ፋ​ሃ​ቸው” ይላል። ናቸው፤
ስለ​ዚህ ምስ​ክ​ር​ህን ወደ​ድሁ።
120መፈ​ራ​ት​ህን በሥ​ጋዬ ውስጥ አስ​ማማ፤
ከፍ​ር​ድህ የተ​ነሣ ፈር​ቻ​ለ​ሁና።
ዔ።
121ፍር​ድ​ንና ጽድ​ቅን ሠራህ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሠራሁ” ይላል።
ለሚ​ያ​ስ​ጨ​ን​ቁኝ አሳ​ል​ፈህ አት​ስ​ጠኝ።
122ባሪ​ያ​ህን በመ​ል​ካም ጠብ​ቀው፤
ትዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችም አይ​ጋ​ፉኝ።
123ዐይ​ኖቼ ለማ​ዳ​ንህ፥
ለጽ​ድ​ቅ​ህም ቃል ፈዘዙ።
124ለባ​ሪ​ያህ እንደ ምሕ​ረ​ትህ አድ​ርግ፥
ፍር​ድ​ህ​ንም አስ​ተ​ም​ረኝ።
125እኔ ባሪ​ያህ ነኝ፤ እን​ዳ​ስ​ተ​ውል አድ​ር​ገኝ፥
ምስ​ክ​ር​ህ​ንም አው​ቃ​ለሁ።
126ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሥራ ጊዜ አለው፥
ሕግ​ህ​ንም ሻሩት።
127ስለ​ዚህ ከወ​ር​ቅና ከዕ​ንቍ ይልቅ ትእ​ዛ​ዝ​ህን ወደ​ድሁ።
128ስለ​ዚህ ወደ ትእ​ዛ​ዝህ ሁሉ አቀ​ናሁ፥
የዐ​መ​ፃ​ንም መን​ገድ ሁሉ ጠላሁ።
ፌ።
129ምስ​ክ​ርህ ድንቅ ነው፤
ስለ​ዚህ ነፍሴ ፈለ​ገ​ችው።
130የቃ​ልህ ነገር ያበ​ራል፥
ሕፃ​ና​ት​ንም አስ​ተ​ዋ​ዮች ያደ​ር​ጋል።
131አፌን ከፈ​ትሁ፥ ልቡ​ና​ዬ​ንም አሰ​ፋሁ፤
ትእ​ዛ​ዝ​ህን ወድ​ጃ​ለ​ሁና።
132ስም​ህን ለሚ​ወ​ድዱ እን​ደ​ም​ታ​ደ​ር​ገው ፍርድ፥
ወደ እኔ ተመ​ል​ከት፥ ይቅ​ርም በለኝ።
133መን​ገ​ዴ​ንና አካ​ሄ​ዴን እንደ ቃልህ አቅና፤
ኀጢ​አ​ትም ሁሉ ድል አይ​ን​ሳኝ።
134ከሰው ቅሚያ አድ​ነኝ፤
ትእ​ዛ​ዝ​ህ​ንም እጠ​ብ​ቃ​ለሁ ።
135በባ​ሪ​ያህ ላይ ፊት​ህን አብራ፥
ፍር​ድ​ህ​ንም አስ​ተ​ም​ረኝ።
136ሕግ​ህን አል​ጠ​በ​ቅ​ሁ​ምና
የውኃ ፈሳሽ ከዐ​ይ​ኖች ፈሰሰ።
ጻዴ።
137አቤቱ፥ አንተ ጻድቅ ነህ፥
ፍር​ድ​ህም ቅን ነው።
138ምስ​ክ​ር​ህን በጽ​ድቅ አዘ​ዝህ፥
እጅ​ግም ቅን ነው።
139ጠላ​ቶቼ ትእ​ዛ​ዝ​ህን ረስ​ተ​ዋ​ልና
የቤ​ትህ ቅን​ዓት አቀ​ለ​ጠኝ።
140ቃልህ እጅግ የጋለ#ዕብ. “የነ​ጠረ” ይላል። ነው፥
ባሪ​ያህ ግን ወደ​ደው።
141እኔ ታና​ሽና የተ​ና​ቅሁ ነኝ፥
ሕግ​ህን ግን አል​ረ​ሳ​ሁም።
142ጽድ​ቅ​ህም የዘ​ለ​ዓ​ለም ጽድቅ ነው፥
ቃል​ህም የታ​መነ ነው።
143መከ​ራና ችግር አገ​ኙኝ፤
ትእ​ዛ​ዝህ ግን ትም​ህ​ርቴ ነው።
144ምስ​ክ​ርህ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እው​ነት ነው፤
እን​ዳ​ስ​ተ​ውል አድ​ር​ገኝ፥ በሕ​ይ​ወ​ትም አኑ​ረኝ።
ቆፍ።
145በፍ​ጹም ልቤ ጮኽሁ፥ አቤቱ ስማኝ፤
ፍር​ድ​ህ​ንም ፈለ​ግሁ።
146ወደ አንተ ጮኽሁ፥ ስማኝ#“ስማኝ” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። አድ​ነ​ኝም።
ምስ​ክ​ር​ህ​ንም ልጠ​ብቅ።
147ወደ ተራ​ሮች ደረ​ስሁ፥ ጮኽ​ሁም።
ቃል​ህን ተስፋ አድ​ር​ጌ​አ​ለ​ሁና።
148ዐይ​ኖቼ ለመ​ማ​ለድ ደረሱ፥
ቃል​ህን እና​ገር ዘንድ።#“ቃል​ህን እና​ገር ዘንድ” የሚ​ለው በዕብ. የለም።
149አቤቱ፥ እንደ ይቅ​ር​ታህ ቃሌን ስማ፤
እንደ ፍር​ድህ ሕያው አድ​ር​ገኝ።
150በዐ​መፃ የከ​በ​ቡኝ ቀረቡ፥
ከሕ​ግህ ግን ራቁ።
151አቤቱ አንተ ቅርብ ነህ፥
መን​ገ​ዶ​ች​ህም ሁሉ የቀኑ ናቸው።
152ለዘ​ለ​ዓ​ለም እንደ መሠ​ረ​ት​ሃ​ቸው
ከቀ​ድሞ ጀምሮ ምስ​ክ​ሮ​ች​ህን ዐወ​ቅሁ።
ሬስ።
153ሕግ​ህን አል​ረ​ሳ​ሁ​ምና
ችግ​ሬን ተመ​ል​ከት፥ አድ​ነ​ኝም።
154ፍር​ዴን ፍረድ አድ​ነ​ኝም፤
ስለ ቃል​ህም ሕያው አድ​ር​ገኝ።
155ሕይ​ወት ከኃ​ጥ​ኣን የራቀ ነው፥
ፍር​ድ​ህን አል​ፈ​ለ​ጉ​ምና።
156አቤቱ፥ ይቅ​ር​ታህ እጅግ የበዛ ነው፤
እንደ ፍር​ድ​ህም ሕያው አድ​ር​ገኝ።
157የከ​በ​ቡ​ኝና ያስ​ጨ​ነ​ቁኝ ብዙ​ዎች ናቸው፤
ከም​ስ​ክ​ርህ ግን ፈቀቅ አላ​ል​ሁም።
158ቃል​ህን አል​ጠ​በ​ቁ​ምና
ሰነ​ፎ​ችን አይቼ አዘ​ንሁ።
159ትእ​ዛ​ዝ​ህን እንደ ወደ​ድሁ ተመ​ል​ከት፤
አቤቱ፥ በይ​ቅ​ር​ታህ ሕያው አድ​ር​ገኝ።
160የቃ​ልህ መጀ​መ​ሪያ እው​ነት ነው፥
ፍር​ድ​ህም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “እው​ነ​ተኛ ፍር​ድ​ህም ...” ይላል። ሁሉ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እው​ነት ነው።
ሣን።
161አለ​ቆች በከ​ንቱ አሳ​ደ​ዱኝ፤
ከቃ​ልህ የተ​ነሣ ግን ልቤ ደን​ገ​ጠ​ብኝ።
162ብዙ ምርኮ እን​ዳ​ገኘ በቃ​ልህ ደስ አለኝ።
163ዐመ​ፃን ጠላሁ ተጸ​የ​ፍ​ሁም፤
ሕግ​ህን ግን ወደ​ድሁ።
164ስለ እው​ነት ፍር​ድህ ሰባት ጊዜ በቀን አመ​ሰ​ግ​ን​ሃ​ለሁ።
165ስም​ህን ለሚ​ወ​ድዱ#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሕግ​ህን ለሚ​ወዱ” ይላል። ብዙ ሰላም ነው፥
ዕን​ቅ​ፋት የለ​ባ​ቸ​ውም።
166አቤቱ፥ ማዳ​ን​ህን ተስፋ አደ​ረ​ግሁ፥
ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህ​ንም ጠበ​ቅሁ።
167ነፍሴ ምስ​ክ​ር​ህን ጠበ​ቀች፥
እጅ​ግም ወደ​ደ​ችው።
168አቤቱ፥ መን​ገ​ዶ​ችህ ሁሉ በፊ​ትህ ናቸ​ውና።
ትእ​ዛ​ዝ​ህ​ንና ምስ​ክ​ር​ህን ጠበ​ቅሁ።
ታው።
169አቤቱ፥ ልመ​ናዬ ወደ አንተ ትቅ​ረብ፤
እንደ ቃል​ህም አስ​ተ​ዋይ አድ​ር​ገኝ።
170አቤቱ፥ ምል​ጃዬ ወደ ፊትህ ትድ​ረስ፤
እንደ ቃል​ህም አድ​ነኝ።
171ፍር​ድ​ህን አስ​ተ​ም​ረ​ኸ​ኛ​ልና
ከን​ፈ​ሮች ምስ​ጋ​ና​ህን ይና​ገ​ራሉ።
172ትእ​ዛ​ዛ​ትህ ሁሉ ጽድቅ ናቸ​ውና፥
አን​ደ​በቴ ቃል​ህን ተና​ገረ።
173ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን ወድ​ጃ​ለ​ሁና
ቀኝህ የሚ​ያ​ድ​ነኝ ይሁን።
174አቤቱ፥ ማዳ​ን​ህን ናፈ​ቅሁ፤
ሕግ​ህም ትም​ህ​ርቴ ነው።
175ነፍሴ ትኑ​ር​ልኝ ላመ​ስ​ግ​ን​ህም፥
ፍር​ድ​ህም ይር​ዳኝ።
176እንደ ጠፋ በግ ተዘ​ነ​ጋሁ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ተበ​ዘ​በ​ዝሁ” ይላል።
ትእ​ዛ​ዛ​ት​ህን አል​ረ​ሳ​ሁ​ምና ባሪ​ያ​ህን ፈል​ገው።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ