መዝሙረ ዳዊት 92
92
በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር።
1እግዚአብሔር ነገሠ፥ ክብሩንም ለበሰ፤
እግዚአብሔር ኀይልን ለበሰ፥ ታጠቀም፤
ዓለምንም እንዳትናወጥ አጸናት።
2አቤቱ፥#“አቤቱ” የሚለው በግእዝ ብቻ። ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የተዘጋጀ ነው፥
አንተም መቼም መች እስከ ዘለዓለም ነህ።
3አቤቱ፥ ወንዞች ከፍ ከፍ አደረጉ፥
ወንዞች ቃሎቻቸውን ከፍ ከፍ አደረጉ።
4ከብዙ ውኆች ድምፅ የተነሣ
የባሕር እንቅስቃሴዋ#ዕብ. “ሞገድ” ይላል። ድንቅ ነው።
ድንቅስ በልዕልና የሚኖር እግዚአብሔር ነው።
5ምስክርህ እጅግ የታመነ ነው፤
አቤቱ፥ እስከ ረዥም ዘመን ድረስ ለቤትህ ምስጋና#ዕብ. “ቅድስና” ይላል። ይገባል።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 92: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መዝሙረ ዳዊት 92
92
በሰንበት ቀን የምስጋና መዝሙር።
1እግዚአብሔር ነገሠ፥ ክብሩንም ለበሰ፤
እግዚአብሔር ኀይልን ለበሰ፥ ታጠቀም፤
ዓለምንም እንዳትናወጥ አጸናት።
2አቤቱ፥#“አቤቱ” የሚለው በግእዝ ብቻ። ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የተዘጋጀ ነው፥
አንተም መቼም መች እስከ ዘለዓለም ነህ።
3አቤቱ፥ ወንዞች ከፍ ከፍ አደረጉ፥
ወንዞች ቃሎቻቸውን ከፍ ከፍ አደረጉ።
4ከብዙ ውኆች ድምፅ የተነሣ
የባሕር እንቅስቃሴዋ#ዕብ. “ሞገድ” ይላል። ድንቅ ነው።
ድንቅስ በልዕልና የሚኖር እግዚአብሔር ነው።
5ምስክርህ እጅግ የታመነ ነው፤
አቤቱ፥ እስከ ረዥም ዘመን ድረስ ለቤትህ ምስጋና#ዕብ. “ቅድስና” ይላል። ይገባል።