መጽ​ሐፈ ሲራክ 1

1
የጥ​በብ መን​ገ​ዶች
1የጥ​በብ ሁሉ መገ​ኛዋ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ነው፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ከእ​ርሱ ጋር ናት።
2የባ​ሕር አሸ​ዋን፥ የዝ​ናም ጠብ​ታን፥ የዘ​ለ​ዓ​ለ​ም​ነት ቀኖ​ች​ንስ ማን ቈጠረ?
3የሰ​ማ​ይን ምጥ​ቀት፥ የም​ድ​ርን ስፋት፥ የባ​ሕ​ርን ጥል​ቀት፥ ጥበ​ብ​ንም ማን መር​ምሮ አገ​ኛ​ቸው?
4ጥበብ ከሁሉ አስ​ቀ​ድሞ ተፈ​ጠ​ረች።
5የጥ​በብ መታ​ሰቧ ከጥ​ንት ጀምሮ ነው።#በግ​ሪ​ክ​ኛው “የጥ​በብ መታ​ሰቧ ከጥ​ንት ጀምሮ ነው” የሚ​ለው በምዕ. 1 ቍ. 4 ውስጥ ነው ግሪ​ክ​ኛው ቍ. 5 የለ​ውም አን​ዳ​ንድ ዘሮች ቍ. 5 ላይ “የጥ​በብ ምንጭ የል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ነው መን​ገ​ዶ​ች​ዋም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የዘ​ለ​ዓ​ለም ትእ​ዛ​ዛት ናቸው” የሚል ይጽ​ፋሉ።
6የጥ​በብ ሥርዋ ለማን ተገ​ለጠ?
7ምክ​ሯ​ንስ ማን ዐወቀ?#በአ​ን​ዳ​ንድ ዘሮች ምዕ. 1 ቍ. 7 ላይ “የጥ​በብ ዕው​ቀት ለማን ተገ​ለ​ጠች የል​ም​ዷ​ንስ ብል​ጽ​ግና ማን ዐወቀ” ይላል።
8ጥበ​በኛ አንድ ነው፥ እጅ​ግም የሚ​ያ​ስ​ፈራ ነው፤
እር​ሱም በዙ​ፋኑ ላይ ጸንቶ ይኖ​ራል።
9እርሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሠራት፤ አያት፥ ሰፈ​ራ​ትም።
በሥ​ራ​ውም ሁሉ ላይ አሳ​ደ​ራት፤
10እር​ስ​ዋም እንደ እርሱ ስጦታ ከሥ​ጋዊ ሁሉ ጋር ናት፥
ለሚ​ወ​ዱ​ትም ሁሉ እር​ስ​ዋን ሰጣ​ቸው።
11እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ክብር ነው፥
የሚ​ያ​ስ​መ​ካም ነው፥ ደስ​ታም ነው፥ የደ​ስታ ዘው​ድም ነው።
12እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት የልብ ደስታ ነው፤
ሐሤ​ት​ንም ይሰ​ጣል፤ ደስም ያሰ​ኛል፥ የሕ​ይ​ወ​ት​ንም ዘመን ያረ​ዝ​ማል።
13እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው ፍጻ​ሜው ያም​ራል፤
በሚ​ሞ​ት​በ​ትም ቀን ይከ​ብ​ራል።
14የጥ​በብ መጀ​መ​ሪያ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው፤
በእ​ና​ታ​ቸው ማኅ​ፀን ከም​እ​መ​ናን ጋር ተፈ​ጠ​ረች።
15ከሰ​ዎ​ችም ጋር የዓ​ለ​ምን መሠ​ረት ፈጠ​ረች፤
ከዘ​ራ​ቸ​ውም ጋር ልት​ኖር ታመ​ነች።
16ጥበ​ብን መጥ​ገብ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው፥
በፍ​ሬ​ዋም ታጠ​ግ​ባ​ቸ​ዋ​ለች።
17በቤ​ቶ​ች​ዋም ደስታ መል​ት​ዋል፥
በቦ​ታ​ዎ​ች​ዋም ፍሬ አለ።#ግሪ​ክ​ኛው “እር​ስዋ ቤቶ​ቻ​ቸ​ውን ሁሉ በደ​ስታ ትሞ​ላ​ለች፥ ጎታ​ዎ​ቻ​ቸ​ው​ንም በም​ርት ትሞ​ላ​ለች” ይላል።
18የጥ​በብ ዘው​ድዋ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው፤
ሰላ​ምን ያመ​ጣ​ታል፥ ይፈ​ው​ሳል፥ ያድ​ና​ልም።
19ፈጣ​ሪዋ አያት፥ ሰፈ​ራ​ትም፥
የም​ክ​ር​ንና የዕ​ው​ቀ​ትን የጥ​በ​ብ​ንም ምንጭ አፈ​ሰሰ፥
የሚ​ያ​ጸ​ኗ​ት​ንም ሰዎች አገ​ነ​ና​ቸው፥ አከ​በ​ራ​ቸ​ውም።
20የጥ​በብ ሥር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው፥
ቅር​ን​ጫ​ፍ​ዋም የሕ​ይ​ወ​ትን ዘመን ያረ​ዝ​ማል።
ከኀ​ጢ​አት ለመ​ራቅ ራስን መቈ​ጣ​ጠር
21በተ​ቈጣ ጊዜ መከራ ይመ​ጣ​በ​ታ​ልና
ቍጡና ዐመ​ፀኛ ሰው መጽ​ደቅ አይ​ች​ልም።
22ጊዜ​ዋን እስ​ክ​ታ​ሳ​ልፍ ድረስ ቍጣን ታገ​ሣት፤
ኋላም ደስ ታሰ​ኝ​ሃ​ለች።
23ጊዜ​ውን እስ​ክ​ታ​ገኝ ድረስ ነገ​ር​ህን ሰውር፤
ብዙ ሰዎ​ችም ጥበ​ብ​ህን ይና​ገ​ራሉ።
24በጥ​በብ መዛ​ግ​ብት የም​ሳሌ ትም​ህ​ርት አለ።
ኀጢ​አ​ተኛ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈ​ራ​ውን ይጸ​የ​ፈ​ዋል።
25ጥበ​ብን ከወ​ደ​ድ​ሃት ትእ​ዛ​ዞ​ቹን ጠብቅ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እር​ስ​ዋን ይሰ​ጥ​ሃል።
26ጥበ​ብም፥ ዕው​ቀ​ትም፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ነው፤
ፈቃ​ዱም ሃይ​ማ​ኖ​ትና የዋ​ሀት ነው።
27እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራ​ትን አት​ዘ​ንጋ።
28እየ​ተ​ጠ​ራ​ጠ​ርህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በሁ​ለት ልብ አታ​ገ​ል​ግ​ለው።
29በሰው አፍ አት​ው​ደቅ፥#ግሪኩ “በሰው ፊት ግብዝ አት​ሁን” ይላል።
ከን​ፈ​ሮ​ች​ህ​ንም ጠብቅ።
30እን​ዳ​ቷ​ረድ ሰው​ነ​ት​ህም እን​ዳ​ት​ወ​ድቅ ራስ​ህን ከፍ ከፍ አታ​ድ​ርግ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሰ​ወ​ር​ኸ​ውን ይገ​ል​ጥ​ብ​ሃል።
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በመ​ፍ​ራት አል​መ​ጣ​ህ​ምና፥ በል​ብ​ህም ሽን​ገላ ሞል​ት​ዋ​ልና
በብ​ዙ​ዎች ሰዎች መካ​ከል ይጥ​ል​ሃል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ