መጽሐፈ ሲራክ 43
43
1የጠራች ጠፈርን በህዋው ላይ አጸናት፤
የሰማይም መታየት በክብሩ ነው።
2ብርሃኑን ያሳይ ዘንድ ፀሐይን ያወጣል፤
የሰማይም ብርሃን ሥርዐቱ ድንቅ ነው ።
3በዋዕዩም ሀገሩን ያቃጥላል፤
ዋዕዩንስ ማን ይቋቋመዋል?
4ዋዕዩንም እሳት እንደሚነድድባት ምድጃ ያደርጋል፤
ፀሐይ ግን ከሦስት ጊዜ በላይ የበለጠ ተራሮችን ያቃጥላቸዋል።
ከእርሱ የሚወጣው እሳታዊ ዋዕይ፥ የሚልከውም ብርሃን ዐይን ያጨልማል፤
5የፈጠረው እግዚአብሔርም ታላቅ ነው፤
በቃሉም ፈጥኖ ይሄዳል።
6ጨረቃም ለሁሉ የዘመን መለኪያ ናት፤
ለዓለምም ሁሉ ምልክት ናት፤ በእርስዋም ቀን ይለያል።
7በጨረቃም የበዓላት ምልክት ይታወቃል፤
ሕፀፅ እያደረገች የምታልቅ ብርሃን እርስዋ ናት።
8ጨረቃስ እንደ ስሟ ናት፤ ዕድገትዋም ድንቅ ነው፤
በሰማይ ሠራዊት ሥርዐትም ሕፀፅንና ምላትን ማፈራረቅዋ ድንቅ ነው፤
በሰማይ ሠራዊት መካከልም ታበራለች።
9የሰማይም ጌጥ የከዋክብት ብርሃን ነው።
በእግዚአብሔር ሰማይ ለዓለም ያበራሉ።
10በቅዱሱም ቃል በየሥርዐታቸው ጸንተው ይኖራሉ፤
ከሥርዐታቸውም ወጥተው አያልፉም።
11ብርሃኑ ፈጽሞ ያማረ ነውና፥
ቀስተ ደመናውን አይተህ ፈጣሪውን አመስግነው።
12በሰማይ ይከፈላል፤
ብርሃኑም ይከበዋል፤
የልዑልም እጅ ይከፍለዋል።
13በትእዛዙ በረድ ይዘንባል፤
መብረቅም በፈቃዱ ፈጥኖ ይወርዳል።
14ስለዚህ ነገር መዛግብቱን ይገልጣል፤
ደመናትም እንደ ወፎች ይበርራሉ።
15በገናናነቱም ደመናትን ያጸናቸዋል፤
የበረድ ድንጋይም ይሰባበራል።
16በመጐብኘቱም ተራሮች ይነዋወጣሉ፤
በፈቃዱም የምሥራቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የደቡብ” ይላል። ነፋስ ይነፍሳል።
17የመብረቁም ድምፅ ምድርን ያስፈራታል፤
የምዕራብም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሰሜን” ይላል። ነፋስ ሰውነትን ያደርቃታል፤
በረድንም እንደሚበርሩ ወፎች ይበትነዋል፤
አወራረዱም እንደ አንበጣ አወራረድ ነው።
18የንጣቱም ውበት ለዐይን ድንቅ ነው፤
መዝነቡም ለልብ ድንቅ ነው።
19በረድን እንደ ጨው ያፈስሰዋልና፤
ጉምንም በምድር ላይ ይበትነዋል፤
ውርጭም ከረጋ በኋላ እንደ ሻፎ የብርሌ ስባሪ ብልጭ ይላል።
20የቀዘቀዘው የምሥራቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሰሜን” ይላል። ነፋስም ይነፍሳል፤
ውርጩም በውኃ ላይ ይረጋል፤
በውኃው መከማቻ ላይም ይቆማል፤
እንደ ብረት ልብስም በውኃ ላይ ይኖራል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ውኃውም እንደ ብረት ልብስ ይለብሰዋል” ይላል። ይሸፍናታልም።
21ተራራውን ይበላል፤
ምድረ በዳውንም ያቃጥላል፤
ሣሩንም እንደ እሳት ያቃጥለዋል።
22የሰው ሁሉ ፈውስ ፈጥኖ የሚመጣ ካፊያ ነው፤
ዝናብም ወደ ምድር በወረደ ጊዜ ደስ ያሰኛል።
23በእርሱም ምክር ጥልቁ ይደርቃል፤
በዚያም ደሴቶችን ተከለ።
24በባሕርም የሚሄዱ ሰዎች መከራዋን ይናገራሉ፥
እኛም ሰምተን እናደንቃለን።
25በዚያም ሥራው ፈጽሞ ድንቅ ነው።
ከብትን መግዛት በየወገኑ ነው።
26ለበጎ መዓዛም ከእርሱ መሥዋዕት ይሠዋለታል፤
በቃሉም ሁሉ ይደረጋል።
27ብዙ ነገርን እንናገራለን፤ መፈጸምም አንችልም፤
ነገር ግን የነገሩ ሁሉ መጨረሻ እርሱ ብቻ ነው።
28ከፍጥረት ሁሉ እርሱ ይበልጣልና፤
እርሱን ማመስገን ምን ያህል እንችላለን?
29እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነው፤
እጅግም ታላቅ ነው፤ ኀይሉም ድንቅ ነው።
30ጨርሳችሁ ማመስገንን አትጠነቅቁምና፤
የተቻላችሁን ያህል እግዚአብሔርን አመስግኑት፤
እርሱ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ነው።
በፍጹም ኀይላችሁም አግንኑት፤
አትደርሱበትምና እርሱን ማመስገንን ቸል አትበሉ።
31እርሱን አይቶ የሚነግረን ማን ነው?
እንደ ገናናነቱስ መጠን ማን ያገነዋል?
32የማይታየው ከዚህ የሚበልጠው ፍጥረቱ ብዙ ነው፤
ነገር ግን ያየነው ፍጥረቱ ጥቂት ብቻ ነው።
33እግዚአብሔር ሁሉን ፈጥሯልና፤
ለጻድቃንም ጥበብን ሰጣቸው።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 43: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 43
43
1የጠራች ጠፈርን በህዋው ላይ አጸናት፤
የሰማይም መታየት በክብሩ ነው።
2ብርሃኑን ያሳይ ዘንድ ፀሐይን ያወጣል፤
የሰማይም ብርሃን ሥርዐቱ ድንቅ ነው ።
3በዋዕዩም ሀገሩን ያቃጥላል፤
ዋዕዩንስ ማን ይቋቋመዋል?
4ዋዕዩንም እሳት እንደሚነድድባት ምድጃ ያደርጋል፤
ፀሐይ ግን ከሦስት ጊዜ በላይ የበለጠ ተራሮችን ያቃጥላቸዋል።
ከእርሱ የሚወጣው እሳታዊ ዋዕይ፥ የሚልከውም ብርሃን ዐይን ያጨልማል፤
5የፈጠረው እግዚአብሔርም ታላቅ ነው፤
በቃሉም ፈጥኖ ይሄዳል።
6ጨረቃም ለሁሉ የዘመን መለኪያ ናት፤
ለዓለምም ሁሉ ምልክት ናት፤ በእርስዋም ቀን ይለያል።
7በጨረቃም የበዓላት ምልክት ይታወቃል፤
ሕፀፅ እያደረገች የምታልቅ ብርሃን እርስዋ ናት።
8ጨረቃስ እንደ ስሟ ናት፤ ዕድገትዋም ድንቅ ነው፤
በሰማይ ሠራዊት ሥርዐትም ሕፀፅንና ምላትን ማፈራረቅዋ ድንቅ ነው፤
በሰማይ ሠራዊት መካከልም ታበራለች።
9የሰማይም ጌጥ የከዋክብት ብርሃን ነው።
በእግዚአብሔር ሰማይ ለዓለም ያበራሉ።
10በቅዱሱም ቃል በየሥርዐታቸው ጸንተው ይኖራሉ፤
ከሥርዐታቸውም ወጥተው አያልፉም።
11ብርሃኑ ፈጽሞ ያማረ ነውና፥
ቀስተ ደመናውን አይተህ ፈጣሪውን አመስግነው።
12በሰማይ ይከፈላል፤
ብርሃኑም ይከበዋል፤
የልዑልም እጅ ይከፍለዋል።
13በትእዛዙ በረድ ይዘንባል፤
መብረቅም በፈቃዱ ፈጥኖ ይወርዳል።
14ስለዚህ ነገር መዛግብቱን ይገልጣል፤
ደመናትም እንደ ወፎች ይበርራሉ።
15በገናናነቱም ደመናትን ያጸናቸዋል፤
የበረድ ድንጋይም ይሰባበራል።
16በመጐብኘቱም ተራሮች ይነዋወጣሉ፤
በፈቃዱም የምሥራቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የደቡብ” ይላል። ነፋስ ይነፍሳል።
17የመብረቁም ድምፅ ምድርን ያስፈራታል፤
የምዕራብም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሰሜን” ይላል። ነፋስ ሰውነትን ያደርቃታል፤
በረድንም እንደሚበርሩ ወፎች ይበትነዋል፤
አወራረዱም እንደ አንበጣ አወራረድ ነው።
18የንጣቱም ውበት ለዐይን ድንቅ ነው፤
መዝነቡም ለልብ ድንቅ ነው።
19በረድን እንደ ጨው ያፈስሰዋልና፤
ጉምንም በምድር ላይ ይበትነዋል፤
ውርጭም ከረጋ በኋላ እንደ ሻፎ የብርሌ ስባሪ ብልጭ ይላል።
20የቀዘቀዘው የምሥራቅ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የሰሜን” ይላል። ነፋስም ይነፍሳል፤
ውርጩም በውኃ ላይ ይረጋል፤
በውኃው መከማቻ ላይም ይቆማል፤
እንደ ብረት ልብስም በውኃ ላይ ይኖራል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ውኃውም እንደ ብረት ልብስ ይለብሰዋል” ይላል። ይሸፍናታልም።
21ተራራውን ይበላል፤
ምድረ በዳውንም ያቃጥላል፤
ሣሩንም እንደ እሳት ያቃጥለዋል።
22የሰው ሁሉ ፈውስ ፈጥኖ የሚመጣ ካፊያ ነው፤
ዝናብም ወደ ምድር በወረደ ጊዜ ደስ ያሰኛል።
23በእርሱም ምክር ጥልቁ ይደርቃል፤
በዚያም ደሴቶችን ተከለ።
24በባሕርም የሚሄዱ ሰዎች መከራዋን ይናገራሉ፥
እኛም ሰምተን እናደንቃለን።
25በዚያም ሥራው ፈጽሞ ድንቅ ነው።
ከብትን መግዛት በየወገኑ ነው።
26ለበጎ መዓዛም ከእርሱ መሥዋዕት ይሠዋለታል፤
በቃሉም ሁሉ ይደረጋል።
27ብዙ ነገርን እንናገራለን፤ መፈጸምም አንችልም፤
ነገር ግን የነገሩ ሁሉ መጨረሻ እርሱ ብቻ ነው።
28ከፍጥረት ሁሉ እርሱ ይበልጣልና፤
እርሱን ማመስገን ምን ያህል እንችላለን?
29እግዚአብሔር የሚያስፈራ ነው፤
እጅግም ታላቅ ነው፤ ኀይሉም ድንቅ ነው።
30ጨርሳችሁ ማመስገንን አትጠነቅቁምና፤
የተቻላችሁን ያህል እግዚአብሔርን አመስግኑት፤
እርሱ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ነው።
በፍጹም ኀይላችሁም አግንኑት፤
አትደርሱበትምና እርሱን ማመስገንን ቸል አትበሉ።
31እርሱን አይቶ የሚነግረን ማን ነው?
እንደ ገናናነቱስ መጠን ማን ያገነዋል?
32የማይታየው ከዚህ የሚበልጠው ፍጥረቱ ብዙ ነው፤
ነገር ግን ያየነው ፍጥረቱ ጥቂት ብቻ ነው።
33እግዚአብሔር ሁሉን ፈጥሯልና፤
ለጻድቃንም ጥበብን ሰጣቸው።