መጽሐፈ ሲራክ 48
48
ነቢዩ ኤልያስ
1ነቢዩ ኤልያስም እንደ እሳት ተነሣ፥
ቃሉም እንደ ነበልባል ያቃጥል ነበር።
2ረኃብንም አመጣባቸው፤
በቅንዓቱም አሳነሳቸው።
3በእግዚአብሔርም ቃል ሰማይን ዘጋው፤
ከሰማይም እሳትን ሦስት ጊዜ አወረደ።
4ኤልያስ ሆይ፥ በተአምራትህ እንዴት ከበርህ!
እንዳንተስ የተመካ ማንነው?
5በልዑል ቃል ከሞቱ ሰዎች ለይቶ ምውትን ከመቃብር ያስነሣ ማንነው?
6ነገሥታቱን ወደ ሞት፥
የከበሩ ሰዎቹንም ከአልጋቸው ያወረዳቸው ማንነው?
7በሲና የእግዚአብሔርን ተግሣጽ፥
በኮሬብም የበቀልን ፍርድ የሰማ ማንነው?
8ይበቀሉ ዘንድ ነገሥታቱን፥
ከእርሱም ቀጥሎ ይተኩ ዘንድ ነቢያትን የቀባቸው ማንነው?
9በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ
ወደ ሰማይ የወጣ ማንነው?
10መቅሠፍቱ ከመውረዱ አስቀድሞ የእግዚአብሔርን ቍጣ ይመልስ ዘንድ፥
የአባትንም ልብ ወደ ልጅ ይመልስ ዘንድ፤
የያዕቆብንም ወገኖች ያጸናቸው ዘንድ በተወሰነ ዘመን የተጻፈለት ማንነው?
11የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ#አንዳንድ የግሪክ ዘርዕ “በፍቅርህ የሞቱ” ይላል። ሰዎች ብፁዓን ናቸው፥
እኛም ስለ አንተ በሕይወት እንኖራለን።
ነቢዩ ኤልሳዕ
12በእሳት ሠረገላ ወደ ላይ የወጣ ኤልያስ ነው፤
ከእርሱም መንፈስ የተመላ ኤልሳዕ ነበረ፤
በዘመኑም አለቆች አላስደነገጡትም፤
ማንም እርሱን የተቋቋመው አልነበረም።
13ከነገሩም ሁሉ የተሳነው አልነበረም፤
ከሞተም በኋላ በድኑ ትንቢትን ተናገረ።
14በሕይወቱም ሳለ ድንቅ ተአምራትን አደረገ፤
በሞቱም ሥራው ድንቅ ነበረ።
15ከዚህም ሁሉ ጋር ሕዝቡ ንስሓ አልገቡም፤
ከሀገራቸውም ተማርከው እስኪሄዱ ድረስ ኀጢአታቸውን አልተዉም፤
በሀገሩም ሁሉ ተበተኑ፤
ከሕዝቡም ጥቂት ሰዎች ቀሩ፤
ገዢም ከዳዊት ቤት ቀረ።
16ከእነርሱም ደግ ሥራ የሠሩ ነበሩ፤
ኀጢአትንም ያበዟት ነበሩ።
ንጉሡ ሕዝቅያስ
17ሕዝቅያስም ከተማውን አጸና
በመካከልዋም ውኃን አስገባ፤
ዓለቱንም በብረት ቈፈረ፤ የውኃ መስኖ አሠራ።
18ሰናክሬምም በዘመኑ ዘመተ፤
ራፋስቂስንም ላከው፤
ወደ እርሱም ሄዶ በጽዮን ላይ እጁን አነሣ፤ ታበየ፤
አፉንም ከፍ ከፍ አድርጎ ተናገረ።
19ያን ጊዜም ልቡናቸው ደነገጠባቸው፤
እጃቸውም ዛለ፤ እንደምትወልድ ሴትም ምጥ ያዛቸው።
20ይቅር ባይ እግዚአብሔርንም ለመኑት፤
እጃቸውንም ወደ እርሱ አነሡ፤
ቅዱሱም ከሰማይ ፈጥኖ ሰማቸው፤
በኢሳይያስም እጅ አዳናቸው።
21የአሦርንም#ግእዝ “ፋርስ” ይላል። ሠራዊት አጠፋ፤
መልአኩም አጠፋቸው።
22ሕዝቅያስ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘው ሥራ ሠርትዋልና፤
በራእዩ ታላቅና ታማኝ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስም እንዳዘዘው
የአባቱ የዳዊትን መንገድ አጽንትዋልና።
23ፀሐይም በዘመኑ ከመሄድ ወደ ኋላ ተመለሰች፤
ለንጉሡም ዘመን ጨመረለት።
24በታላቅ መንፈስም በመጨረሻ የሚሆነውን አየ፤
በጽዮን የሚያለቅሱትንም አጽናናቸው።
25ለዘለዓለሙ የሚሆነውን፥
የተሰወረውንም ሳይሆን ተናገረ።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 48: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 48
48
ነቢዩ ኤልያስ
1ነቢዩ ኤልያስም እንደ እሳት ተነሣ፥
ቃሉም እንደ ነበልባል ያቃጥል ነበር።
2ረኃብንም አመጣባቸው፤
በቅንዓቱም አሳነሳቸው።
3በእግዚአብሔርም ቃል ሰማይን ዘጋው፤
ከሰማይም እሳትን ሦስት ጊዜ አወረደ።
4ኤልያስ ሆይ፥ በተአምራትህ እንዴት ከበርህ!
እንዳንተስ የተመካ ማንነው?
5በልዑል ቃል ከሞቱ ሰዎች ለይቶ ምውትን ከመቃብር ያስነሣ ማንነው?
6ነገሥታቱን ወደ ሞት፥
የከበሩ ሰዎቹንም ከአልጋቸው ያወረዳቸው ማንነው?
7በሲና የእግዚአብሔርን ተግሣጽ፥
በኮሬብም የበቀልን ፍርድ የሰማ ማንነው?
8ይበቀሉ ዘንድ ነገሥታቱን፥
ከእርሱም ቀጥሎ ይተኩ ዘንድ ነቢያትን የቀባቸው ማንነው?
9በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ
ወደ ሰማይ የወጣ ማንነው?
10መቅሠፍቱ ከመውረዱ አስቀድሞ የእግዚአብሔርን ቍጣ ይመልስ ዘንድ፥
የአባትንም ልብ ወደ ልጅ ይመልስ ዘንድ፤
የያዕቆብንም ወገኖች ያጸናቸው ዘንድ በተወሰነ ዘመን የተጻፈለት ማንነው?
11የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ#አንዳንድ የግሪክ ዘርዕ “በፍቅርህ የሞቱ” ይላል። ሰዎች ብፁዓን ናቸው፥
እኛም ስለ አንተ በሕይወት እንኖራለን።
ነቢዩ ኤልሳዕ
12በእሳት ሠረገላ ወደ ላይ የወጣ ኤልያስ ነው፤
ከእርሱም መንፈስ የተመላ ኤልሳዕ ነበረ፤
በዘመኑም አለቆች አላስደነገጡትም፤
ማንም እርሱን የተቋቋመው አልነበረም።
13ከነገሩም ሁሉ የተሳነው አልነበረም፤
ከሞተም በኋላ በድኑ ትንቢትን ተናገረ።
14በሕይወቱም ሳለ ድንቅ ተአምራትን አደረገ፤
በሞቱም ሥራው ድንቅ ነበረ።
15ከዚህም ሁሉ ጋር ሕዝቡ ንስሓ አልገቡም፤
ከሀገራቸውም ተማርከው እስኪሄዱ ድረስ ኀጢአታቸውን አልተዉም፤
በሀገሩም ሁሉ ተበተኑ፤
ከሕዝቡም ጥቂት ሰዎች ቀሩ፤
ገዢም ከዳዊት ቤት ቀረ።
16ከእነርሱም ደግ ሥራ የሠሩ ነበሩ፤
ኀጢአትንም ያበዟት ነበሩ።
ንጉሡ ሕዝቅያስ
17ሕዝቅያስም ከተማውን አጸና
በመካከልዋም ውኃን አስገባ፤
ዓለቱንም በብረት ቈፈረ፤ የውኃ መስኖ አሠራ።
18ሰናክሬምም በዘመኑ ዘመተ፤
ራፋስቂስንም ላከው፤
ወደ እርሱም ሄዶ በጽዮን ላይ እጁን አነሣ፤ ታበየ፤
አፉንም ከፍ ከፍ አድርጎ ተናገረ።
19ያን ጊዜም ልቡናቸው ደነገጠባቸው፤
እጃቸውም ዛለ፤ እንደምትወልድ ሴትም ምጥ ያዛቸው።
20ይቅር ባይ እግዚአብሔርንም ለመኑት፤
እጃቸውንም ወደ እርሱ አነሡ፤
ቅዱሱም ከሰማይ ፈጥኖ ሰማቸው፤
በኢሳይያስም እጅ አዳናቸው።
21የአሦርንም#ግእዝ “ፋርስ” ይላል። ሠራዊት አጠፋ፤
መልአኩም አጠፋቸው።
22ሕዝቅያስ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘው ሥራ ሠርትዋልና፤
በራእዩ ታላቅና ታማኝ የነበረው ነቢዩ ኢሳይያስም እንዳዘዘው
የአባቱ የዳዊትን መንገድ አጽንትዋልና።
23ፀሐይም በዘመኑ ከመሄድ ወደ ኋላ ተመለሰች፤
ለንጉሡም ዘመን ጨመረለት።
24በታላቅ መንፈስም በመጨረሻ የሚሆነውን አየ፤
በጽዮን የሚያለቅሱትንም አጽናናቸው።
25ለዘለዓለሙ የሚሆነውን፥
የተሰወረውንም ሳይሆን ተናገረ።