መጽሐፈ ሲራክ 6
6
1ጠላት ከምትሆን ወዳጅ ሁን፤
የክፉ ስም ፍጻሜው ስድብና ውርደት ነውና፤
ምላሱ ሁለት የሆነ ኀጢአተኛ ሰውም እንዲህ ነው።
2ከልቡናህ ባነቃኸውም ምክር ራስህን ከፍ ከፍ አታድርግ፤
አንበሳ ላምን እንደሚነጣጠቅ ሰውነትህን እንዳይነጥቋት።
3ቅጠልህን ይበላብሃል፥ ፍሬህንም ታጣለህ፤
እንደ ደረቅ እንጨትም ይጥልሃል።
4ክፉ ሰውነት ገንዘብ ያደረጋትን ሰው ታጠፋዋለች፤
ጠላቱንም በእርሱ የጨከነ ታደርገዋለች።
እውነተኛና እውነተኛ ያልሆነ ጓደኝነት
5ልዝብ አንደበት ወንድማማችነትን ያበዛል፤
ልዝብ አፍም ወዳጅን ያበዛል።
6ብዙ ሰዎች ወዳጆች ይሁኑህ፤
ነገር ግን ከብዙዎቹ አንዱ ምክርህን የምትገልጥለት ይሁን።
7ወዳጅ ብታበጅ በችግርህ ወራት ወዳጅ አብጅ።
ፈጥነህም እምነት አትጣልበት፤
8ለጥቂት ቀን የሚሆን ወረተኛ ወዳጅ አለና፤
በመከራህም ጊዜ ከአንተ ጋራ አይታገሥም።
9ጠላት የሚሆንህና፥ የሚሰድብህ፥
ሰውረህ የሠራኸውን ኀጢአትህንም የሚገልጥብህ ወዳጅ አለ።
10ስለ ማዕድህም የሚወድህ ወዳጅ አለ፤
እርሱም ከአንተ ጋራ አይኖርም፥
በተቸገርህም ጊዜ ይለይሃል።
11ባለጸጋ በሆንህ ጊዜ እንዳንተ ይሆናል፤
ቤተ ሰብህንም ይገዛል።
12ብትቸገር ግን እርሱ ባላጋራህ ይሆናል፤
እንዳታየውም ይሰወርሃል።
13ከጠላቶችህ ራቅ፥
ወዳጆችህንም ተጠባበቃቸው።
14የታመነ ወዳጅ እንደ ጸና አላባሽ አግሬ ጋሻ ነው፤
እርሱን ያገኘ ሰው ድልብ አገኘ።
15ለታመነ ወዳጅ ለውጥ የለውም፤
ለደግነቱም ሚዛን የለውም።
16የታመነ ወዳጅ የሕይወት መድኀኒት ነው፤
እግዚአብሔርንም የሚፈሩ ያገኙታል።
17እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ወዳጅነቱን ያጸናል፤
ባልንጀራው እንደ እርሱ ይሆነዋልና።
የጥበብ በረከት
18ልጄ ሆይ፥ በሕፃንነትህ ጥበብን ምረጣት፤
እስክታረጅም ድረስ ታገኛታለህ።
19እንደሚያርስና እንደሚዘራ ሰው ወደ እርስዋ ሂድ፤
የተባረከ ፍሬዋንም ጠብቅ፤
ስለ እርስዋ በመሥራት ጥቂት ትደክማለህ፤
ነገር ግን ፈጥነህ ፍሬዋን ትበላለህ።
20በሰነፎች ዘንድ ፈጽማ ጐፃጕፅ ናት፤
አእምሮ በሌለው ሰውም አታድርም።
21የፈተና ድንጋይ አንሥተው በተሸከሙት ጊዜ እንዲከብድ፥
እንደዚሁ ትከብደዋለች፤ ፈጥኖም ይጥላታል።
22ጥበብስ እንደ ስሟ ናት፤
ብዙ ሰዎችም የሚያውቋት አይደሉም።
23ልጄ ሆይ፥ ስማኝ፥ በምክሬም ጽና፤
ምክሬንም አታቃልል።
24እግሮችህን ወደ ቀምበርዋ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ወደ እግር ብረቷ” ይላል። አግባ፤
ዛንጅርዋንም ባንገትህ እሰር።
25ጫንቃህን ዝቅ አድርገህ ተሸከማት፤
በእግር ብረትዋም አትበሳጭ።
26በፍጹም ነፍስህ ወደ እርሷ ተሰማራ፥
በፍጹም ኀይልህም መንገድዋን ጠብቅ።
27ፍለጋዋን ተከተል፥ ፈልጋት፤ ታገኛታለህም።
ያዛት፥ አትተዋትም።
28በፍጻሜህም ዕረፍትን ታገኛለህ፤
ደስታም ይሆንሃል።
29እግር ብረትዋም እንደ ጽኑ ጋሻ ይሆንልሃል፤
ዛንጅርዋም የክብር ልብስ ወደ መሆን ይመለስልሃል።
30የዘለዓለም ወርቅ በእርሷ ዘንድ አለና፤
ማሰሪያዋም የሰማያዊ ሐር ጌጥ ይሆንሃል።
31እንደ ክብር ልብስ ትለብሳታለህ፥
የደስታ ዘውድንም ታቀዳጅሃለች።
32ልጄ ሆይ፥ ብልህ ትሆን ዘንድ ብትወድድ፥
ትማርም ዘንድ በልቡናህ ብትጨክን፥
33ትሰማ ዘንድ ብትወድም ታገሥ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ዕውቀትን ታገኛለህ” ይላል።
ጆሮህንም ብታዘነብል ብልህ ትሆናለህ።
34በብዙ ሽማግሌዎች ዘንድ ቁም፤
ከእነርሱም ዐዋቂ ሰው ብታይ ተከተለው።
35የመጽሐፉን ነገር ሁሉ ፈጥነህ ስማ፤
የጥበብም ምሳሌ አይዘንጋህ።
36ብልህ ሰው ብታይ ፈጥነህ ወደ እርሱ ሂድ፤
እግርህም በደጃፉ መድረክ ይመላለስ።
37የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ዐስብ፤
መጻሕፍቱንም ሁልጊዜ አንብብ፥
እርሱም ልቡናህን ያጸናዋል፤
ጥበብንም ትወዳት ዘንድ ይሰጥሃል።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 6: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 6
6
1ጠላት ከምትሆን ወዳጅ ሁን፤
የክፉ ስም ፍጻሜው ስድብና ውርደት ነውና፤
ምላሱ ሁለት የሆነ ኀጢአተኛ ሰውም እንዲህ ነው።
2ከልቡናህ ባነቃኸውም ምክር ራስህን ከፍ ከፍ አታድርግ፤
አንበሳ ላምን እንደሚነጣጠቅ ሰውነትህን እንዳይነጥቋት።
3ቅጠልህን ይበላብሃል፥ ፍሬህንም ታጣለህ፤
እንደ ደረቅ እንጨትም ይጥልሃል።
4ክፉ ሰውነት ገንዘብ ያደረጋትን ሰው ታጠፋዋለች፤
ጠላቱንም በእርሱ የጨከነ ታደርገዋለች።
እውነተኛና እውነተኛ ያልሆነ ጓደኝነት
5ልዝብ አንደበት ወንድማማችነትን ያበዛል፤
ልዝብ አፍም ወዳጅን ያበዛል።
6ብዙ ሰዎች ወዳጆች ይሁኑህ፤
ነገር ግን ከብዙዎቹ አንዱ ምክርህን የምትገልጥለት ይሁን።
7ወዳጅ ብታበጅ በችግርህ ወራት ወዳጅ አብጅ።
ፈጥነህም እምነት አትጣልበት፤
8ለጥቂት ቀን የሚሆን ወረተኛ ወዳጅ አለና፤
በመከራህም ጊዜ ከአንተ ጋራ አይታገሥም።
9ጠላት የሚሆንህና፥ የሚሰድብህ፥
ሰውረህ የሠራኸውን ኀጢአትህንም የሚገልጥብህ ወዳጅ አለ።
10ስለ ማዕድህም የሚወድህ ወዳጅ አለ፤
እርሱም ከአንተ ጋራ አይኖርም፥
በተቸገርህም ጊዜ ይለይሃል።
11ባለጸጋ በሆንህ ጊዜ እንዳንተ ይሆናል፤
ቤተ ሰብህንም ይገዛል።
12ብትቸገር ግን እርሱ ባላጋራህ ይሆናል፤
እንዳታየውም ይሰወርሃል።
13ከጠላቶችህ ራቅ፥
ወዳጆችህንም ተጠባበቃቸው።
14የታመነ ወዳጅ እንደ ጸና አላባሽ አግሬ ጋሻ ነው፤
እርሱን ያገኘ ሰው ድልብ አገኘ።
15ለታመነ ወዳጅ ለውጥ የለውም፤
ለደግነቱም ሚዛን የለውም።
16የታመነ ወዳጅ የሕይወት መድኀኒት ነው፤
እግዚአብሔርንም የሚፈሩ ያገኙታል።
17እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ወዳጅነቱን ያጸናል፤
ባልንጀራው እንደ እርሱ ይሆነዋልና።
የጥበብ በረከት
18ልጄ ሆይ፥ በሕፃንነትህ ጥበብን ምረጣት፤
እስክታረጅም ድረስ ታገኛታለህ።
19እንደሚያርስና እንደሚዘራ ሰው ወደ እርስዋ ሂድ፤
የተባረከ ፍሬዋንም ጠብቅ፤
ስለ እርስዋ በመሥራት ጥቂት ትደክማለህ፤
ነገር ግን ፈጥነህ ፍሬዋን ትበላለህ።
20በሰነፎች ዘንድ ፈጽማ ጐፃጕፅ ናት፤
አእምሮ በሌለው ሰውም አታድርም።
21የፈተና ድንጋይ አንሥተው በተሸከሙት ጊዜ እንዲከብድ፥
እንደዚሁ ትከብደዋለች፤ ፈጥኖም ይጥላታል።
22ጥበብስ እንደ ስሟ ናት፤
ብዙ ሰዎችም የሚያውቋት አይደሉም።
23ልጄ ሆይ፥ ስማኝ፥ በምክሬም ጽና፤
ምክሬንም አታቃልል።
24እግሮችህን ወደ ቀምበርዋ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ወደ እግር ብረቷ” ይላል። አግባ፤
ዛንጅርዋንም ባንገትህ እሰር።
25ጫንቃህን ዝቅ አድርገህ ተሸከማት፤
በእግር ብረትዋም አትበሳጭ።
26በፍጹም ነፍስህ ወደ እርሷ ተሰማራ፥
በፍጹም ኀይልህም መንገድዋን ጠብቅ።
27ፍለጋዋን ተከተል፥ ፈልጋት፤ ታገኛታለህም።
ያዛት፥ አትተዋትም።
28በፍጻሜህም ዕረፍትን ታገኛለህ፤
ደስታም ይሆንሃል።
29እግር ብረትዋም እንደ ጽኑ ጋሻ ይሆንልሃል፤
ዛንጅርዋም የክብር ልብስ ወደ መሆን ይመለስልሃል።
30የዘለዓለም ወርቅ በእርሷ ዘንድ አለና፤
ማሰሪያዋም የሰማያዊ ሐር ጌጥ ይሆንሃል።
31እንደ ክብር ልብስ ትለብሳታለህ፥
የደስታ ዘውድንም ታቀዳጅሃለች።
32ልጄ ሆይ፥ ብልህ ትሆን ዘንድ ብትወድድ፥
ትማርም ዘንድ በልቡናህ ብትጨክን፥
33ትሰማ ዘንድ ብትወድም ታገሥ፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ዕውቀትን ታገኛለህ” ይላል።
ጆሮህንም ብታዘነብል ብልህ ትሆናለህ።
34በብዙ ሽማግሌዎች ዘንድ ቁም፤
ከእነርሱም ዐዋቂ ሰው ብታይ ተከተለው።
35የመጽሐፉን ነገር ሁሉ ፈጥነህ ስማ፤
የጥበብም ምሳሌ አይዘንጋህ።
36ብልህ ሰው ብታይ ፈጥነህ ወደ እርሱ ሂድ፤
እግርህም በደጃፉ መድረክ ይመላለስ።
37የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ዐስብ፤
መጻሕፍቱንም ሁልጊዜ አንብብ፥
እርሱም ልቡናህን ያጸናዋል፤
ጥበብንም ትወዳት ዘንድ ይሰጥሃል።