መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን 5
5
1እኅቴ ሙሽሪት ሆይ፥ ወደ ገነቴ ገባሁ፥
ከርቤዬን ከሽቱዬ ጋር ለቀምሁ፥
እንጀራዬን ከማሬ ጋር በላሁ፥
የወይን ጠጄን ከወተቴ ጋር ጠጣሁ።
ባልንጀሮች በሉ፥ ጠገቡም፤#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. 2ኛ መደብ ነው።
የወንድሞች ልጆች ጠጡ፥
ሰከሩም፥ ልባቸው የጠፋ ነውና።
2እኔ ተኝቼ ነበር፥ ልቤ ግን ነቅታ ነበር፤
ልጅ ወንድሜ ቃል ደጅ እየመታ መጣ፥
እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥
በራሴ ጠል፥ በቍንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ
ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
3ቀሚሴን አወለቅሁ፥ እንዴት እለብሰዋለሁ?
እግሬን ታጠብሁ፥ እንዴት አሳድፈዋለሁ?
4ልጅ ወንድሜ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥
አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከች።
5ለልጅ ወንድሜ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ፤
እጆች በደጁ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥
ጣቶች ፈሳሹን ከርቤ አንጠባጠቡ።
6ለልጅ ወንድሜ ከፈትሁለት፥
ልጅ ወንድሜ ግን ሂዶ ነበር።
ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች፤
ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም፤
ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
7ከተማዪቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤
መቱኝ፥ አቈሰሉኝም፤
ቅጥር ጠባቂዎችም የዐይነ ርግብ መሸፈኛዬን ከራሴ ላይ ወሰዱት።
8እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥
በምድረ በዳ ኀይልና ጽንዐት አምላችኋለሁ፤
ልጅ ወንድሜን ያገኛችሁት እንደ ሆነ፥
እኔ ከፍቅር የተነሣ መታመሜን ትነግሩት ዘንድ።
9አንቺ በሴቶች ዘንድ የተዋብሽ ሆይ፥
ከወንድሞች ልጆች ይልቅ ልጅ ወንድምሽ ማን ነው?
ይህን ያህል መሐላ አምለሽናልና
ከወንድሞች ልጆች ይልቅ ልጅ ወንድምሽ ማን ነው?
10ወንድሜ ነጭና ቀይ ነው፥
ከአእላፍ የተመረጠ ነው።
11ራሱ ምዝምዝ ወርቅ ነው፤
ቈንዳላው የተዝረፈረፈ ነው፥
እንደ ቍራ ጥቍረትም ጥቁር ነው።
12ዐይኖቹ በሙሉ የውኃ ኵሬ አጠገብ እንዳሉ
በወተት እንደ ታጠቡ በኵሬ ውኃ አጠገብ እንደ ተቀመጡ፥
እንደ ርግቦች ናቸው።
13ጕንጮቹ ሽቱን የሚያፈስሱ የሽቱ መደብ ናቸው።
ከንፈሮቹ እንደ አበቦች ናቸው፥
የሚፈስስ ከርቤንም ያንጠባጥባሉ።
14እጆቹ የተርሴስ ፈርጥ እንዳለባቸው እንደ ለዘቡ የወርቅ ቀለበቶች ናቸው፤
ሆዱ በሰንፔር ዕንቍ እንዳጌጠ እንደ ዝሆን ጥርስ ነው፥
15እግሮቹ በምዝምዝ ወርቅ እንደ ተመሠረቱ
እንደ ዕብነ በረድ ምሰሶዎች ናቸው፤
መልኩ እንደ ሊባኖስና#ግእዝ “ስሂን” ይላል። እንደ ዝግባ ዛፍ የተመረጠ ነው።
16ጕሮሮው እጅግ ጣፋጭ ነው፥ ሁለንተናውም የተወደደ ነው፤
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥
ልጅ ወንድሜ ይህ ነው፥ ወዳጄም ይህ ነው።
Currently Selected:
መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን 5: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን 5
5
1እኅቴ ሙሽሪት ሆይ፥ ወደ ገነቴ ገባሁ፥
ከርቤዬን ከሽቱዬ ጋር ለቀምሁ፥
እንጀራዬን ከማሬ ጋር በላሁ፥
የወይን ጠጄን ከወተቴ ጋር ጠጣሁ።
ባልንጀሮች በሉ፥ ጠገቡም፤#ዕብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. 2ኛ መደብ ነው።
የወንድሞች ልጆች ጠጡ፥
ሰከሩም፥ ልባቸው የጠፋ ነውና።
2እኔ ተኝቼ ነበር፥ ልቤ ግን ነቅታ ነበር፤
ልጅ ወንድሜ ቃል ደጅ እየመታ መጣ፥
እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥
በራሴ ጠል፥ በቍንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ
ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
3ቀሚሴን አወለቅሁ፥ እንዴት እለብሰዋለሁ?
እግሬን ታጠብሁ፥ እንዴት አሳድፈዋለሁ?
4ልጅ ወንድሜ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥
አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከች።
5ለልጅ ወንድሜ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ፤
እጆች በደጁ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥
ጣቶች ፈሳሹን ከርቤ አንጠባጠቡ።
6ለልጅ ወንድሜ ከፈትሁለት፥
ልጅ ወንድሜ ግን ሂዶ ነበር።
ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች፤
ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም፤
ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
7ከተማዪቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤
መቱኝ፥ አቈሰሉኝም፤
ቅጥር ጠባቂዎችም የዐይነ ርግብ መሸፈኛዬን ከራሴ ላይ ወሰዱት።
8እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥
በምድረ በዳ ኀይልና ጽንዐት አምላችኋለሁ፤
ልጅ ወንድሜን ያገኛችሁት እንደ ሆነ፥
እኔ ከፍቅር የተነሣ መታመሜን ትነግሩት ዘንድ።
9አንቺ በሴቶች ዘንድ የተዋብሽ ሆይ፥
ከወንድሞች ልጆች ይልቅ ልጅ ወንድምሽ ማን ነው?
ይህን ያህል መሐላ አምለሽናልና
ከወንድሞች ልጆች ይልቅ ልጅ ወንድምሽ ማን ነው?
10ወንድሜ ነጭና ቀይ ነው፥
ከአእላፍ የተመረጠ ነው።
11ራሱ ምዝምዝ ወርቅ ነው፤
ቈንዳላው የተዝረፈረፈ ነው፥
እንደ ቍራ ጥቍረትም ጥቁር ነው።
12ዐይኖቹ በሙሉ የውኃ ኵሬ አጠገብ እንዳሉ
በወተት እንደ ታጠቡ በኵሬ ውኃ አጠገብ እንደ ተቀመጡ፥
እንደ ርግቦች ናቸው።
13ጕንጮቹ ሽቱን የሚያፈስሱ የሽቱ መደብ ናቸው።
ከንፈሮቹ እንደ አበቦች ናቸው፥
የሚፈስስ ከርቤንም ያንጠባጥባሉ።
14እጆቹ የተርሴስ ፈርጥ እንዳለባቸው እንደ ለዘቡ የወርቅ ቀለበቶች ናቸው፤
ሆዱ በሰንፔር ዕንቍ እንዳጌጠ እንደ ዝሆን ጥርስ ነው፥
15እግሮቹ በምዝምዝ ወርቅ እንደ ተመሠረቱ
እንደ ዕብነ በረድ ምሰሶዎች ናቸው፤
መልኩ እንደ ሊባኖስና#ግእዝ “ስሂን” ይላል። እንደ ዝግባ ዛፍ የተመረጠ ነው።
16ጕሮሮው እጅግ ጣፋጭ ነው፥ ሁለንተናውም የተወደደ ነው፤
እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥
ልጅ ወንድሜ ይህ ነው፥ ወዳጄም ይህ ነው።