መጽ​ሐፈ ጥበብ 2

2
ስለ ክፉ አሳብ
1የቀና ነገ​ርን ሳያ​ስቡ ራሳ​ቸው እን​ዲህ አሉ፥ ሕይ​ወ​ታ​ችን ጥቂት ነው፥ የሚ​ያ​ሳ​ዝ​ንም ነው-። ለሰ​ውም ሞት መድ​ኀ​ኒት የለ​ውም፥ ከመ​ቃ​ብ​ርም የተ​መ​ለሰ የታ​ወቀ የለ​ምና። 2እኛ በከ​ንቱ ተፈ​ጥ​ረ​ና​ልና ከዚ​ህም በኋላ እን​ዳ​ል​ተ​ፈ​ጠ​ርን እን​ሆ​ና​ለን፤ በአ​ፍ​ን​ጫ​ችን ያለ ትን​ፋ​ሻ​ችን እንደ ጢስ ነውና። በል​ቡ​ና​ች​ንም እን​ቅ​ስ​ቃሴ የብ​ል​ጭ​ል​ጭታ ቃል አለና። 3ከሞተ በኋላ ሥጋ​ችን ትቢያ ይሆ​ናል፤ መን​ፈ​ሳ​ች​ንም እንደ ጉም ተን ይበ​ተ​ና​ልና። 4ስማ​ች​ንም በጊዜ ይዘ​ነ​ጋል፤ ሥራ​ች​ን​ንም የሚ​ያ​ስ​በው ማንም የለም፤ ሕይ​ወ​ታ​ች​ንም እንደ ደመና ፍለጋ ያል​ፋል፤ እንደ ጉምም ይበ​ተ​ናል፤ በፀ​ሐይ ጨረር እንደ ተበ​ተነ፥ በሙ​ቀ​ቱም እንደ ቀለጠ ውርጭ ይሆ​ናል።
5ሕይ​ወ​ታ​ች​ንም እንደ ጥላ ያል​ፋ​ልና፥ ይህ የተ​ወ​ሰነ ነገር ስለ​ሆነ ለሞ​ታ​ችን መከ​ል​ከል የለ​ውም፤ ማንም አይ​መ​ል​ሰ​ው​ምና። 6ኑ ባለው መል​ካም ነገር ደስ​ታን እና​ድ​ርግ፤ በጐ​ል​ማ​ሳ​ነ​ታ​ች​ንም ወራት ሳለን በመ​ት​ጋት በሰ​ው​ነ​ታ​ችን ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኘ​ውን እና​ድ​ርግ። 7ዋጋው ብዙ የሆነ ወይን እን​ጠጣ፤ የሚ​ሸት ሽቱ​ንም እን​ቀባ፤ የመ​ፀው አበ​ባም አይ​ለ​ፈን። 8ቡቃ​ያ​ችን ሳይ​ጠ​ወ​ልግ ጽጌ​ረ​ዳን እን​ቀ​ዳጅ፤ ከት​ዕ​ቢ​ታ​ችን አበባ የማ​ይ​ሳ​ተፍ ማንም አይ​ኑር። 9ከእኛ መካ​ከል ደስ​ታ​ችን የማ​ይ​ገ​ባው ሰው አይ​ኑር፤ እርሱ ዕድ​ላ​ችን፥ ርስ​ታ​ች​ንም ነውና በየ​ቦ​ታው ለደ​ስ​ታ​ችን ምል​ክት እን​ተው።
10ጻድ​ቁን ድሃ እን​ቀማ፤ ለባ​ል​ቴ​ቲ​ቱም አን​ራራ፤ ዕድ​ሜው ብዙ ከሆነ ከሽ​ማ​ግ​ሌም ሽበት የተ​ነሣ አን​ፈር። 11ኀይ​ላ​ችን የጽ​ድቅ ሕግ ይሁ​ነን፤ ደካማ ሕሊና የተ​ናቀ ይባ​ላ​ልና።
12ኑ፤ ጻድ​ቁን እን​ግ​ደ​ለው፤ በእኛ ጭን​ቅና ጽኑዕ ሆኖ​ብ​ና​ልና፥ ሥራ​ች​ን​ንም ይቃ​ወ​ማ​ልና፤ ሕግ በማ​ጣ​ታ​ች​ንም ያሽ​ሟ​ጥ​ጠ​ና​ልና፥ የት​ም​ህ​ር​ታ​ች​ን​ንም በደል ይሰ​ብ​ካ​ልና። 13“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ማወቅ በእኔ አለ” ይላል፤ ራሱ​ንም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ልጅ ያደ​ር​ጋል። 14ሕሊ​ና​ች​ን​ንም የሚ​ዘ​ልፍ ሆኖ​ብ​ናል። 15በመ​ል​ኩም በእኛ ጭንቅ ሆኖ​ብ​ናል፤ አኗ​ኗ​ሩም ከሌላ ጋር አይ​መ​ሳ​ሰ​ልም፤ መን​ገ​ዱም ልዩ ነው። 16በእ​ርሱ ዘን​ድም የተ​ና​ቅን ሆነ​ናል፤ ከር​ኵ​ሰ​ትም እን​ደ​ሚ​ርቅ ከመ​ን​ገ​ዳ​ችን ይር​ቃል። የጻ​ድ​ቃ​ንን መጨ​ረሻ ያመ​ሰ​ግ​ናል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አባቱ እንደ ሆነ ይመ​ካል።
17ነገ​ሩም ቀዋሚ እንደ ሆነ እንይ፥ ከመ​ል​ኩም የተ​ነሣ የሚ​ሆ​ነ​ውን እን​መ​ር​ምር።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፍጻ​ሜው ምን እንደ ሆነ እን​መ​ል​ከት” ይላል። 18የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርስ እው​ነ​ተኛ ልጅ ከሆነ ያድ​ነው፤ ከሚ​ቃ​ወ​ሙ​ትም እጅ ይታ​ደ​ገው። 19ቅን​ነ​ቱ​ንም እና​ውቅ ዘንድ በስ​ድ​ብና በመ​ከራ እን​መ​ር​ም​ረው። ትዕ​ግ​ሥ​ቱ​ንም በክፉ እን​ፈ​ት​ነው። 20እንደ ቃሉ ረዳት ይሆ​ነው እንደ ሆነ የከ​ፋና የተ​ዋ​ረደ ሞትን እን​ፍ​ረ​ድ​በት።
ክፋት ልብን እን​ደ​ሚ​ያ​ሳ​ውር
21ይህን ነገር አሰቡ፤ በዚ​ህም ሳቱ፤ ክፋ​ታ​ቸው የልብ ዕው​ሮች አድ​ር​ጋ​ቸ​ዋ​ለ​ችና። 22የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምሥ​ጢር አላ​ወ​ቁም፤ የጻ​ድ​ቁ​ንም ዋጋ ተስፋ አላ​ደ​ረ​ጉም፤ ነውር የሌ​ለ​ባ​ቸ​ውን የን​ጹ​ሐት ነፍ​ሳ​ት​ንም ብዙ ክብር አላ​ወ​ቁም።
23እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰውን ያለ ሞት ፈጥ​ሮ​ታ​ልና፥ በራ​ሱም አም​ሳል ፈጥ​ሮ​ታ​ልና። 24ነገር ግን በዲ​ያ​ብ​ሎስ ቅን​ዐት ሞት መጣ፥ ወደ​ዚህ ዓለ​ምም ገባ። 25ከእ​ር​ሱም ድርሻ የሆ​ኑት ሞትን ሞከ​ሩት።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ