መጽ​ሐፈ ጥበብ 4

4
1ከበ​ጎ​ነት ጋር አለ​መ​ው​ለድ ፍጹም ሥራ ነው፤ በእ​ግ​አ​ብ​ሔር ዘንድ፥ በሰ​ውም ዘንድ የታ​ወ​ቀች ስለ ሆነች ስም አጠ​ራሯ ሕይ​ወት ነውና። 2በዚህ ዓለም ሳለ​ችም ያከ​ብ​ሯ​ታል፤ ካለ​ፈ​ችም በኋላ ፈጽ​መው ይወ​ድ​ዷ​ታል፤ በዚ​ህም ዓለም የገ​ድል ድልን እግ​ኝታ፥ የማ​ያ​ልፍ አክ​ሊ​ል​ንም ተቀ​ዳ​ጅታ ትኖ​ራ​ለች።
3የክ​ፉ​ዎች ሰዎች ልጆች ብዛት አይ​ረ​ባም፤ የከ​ንቱ ተክ​ልም ሥሯ አይ​ታ​ወ​ቅም፤ ጽኑ አኗ​ኗ​ርም አታ​ደ​ር​ግም። 4ለጊ​ዜ​ውም በቅ​ር​ን​ጫ​ፎ​ችዋ ላይ ቅጠል ቢወጣ ሳያ​ድግ ነፋስ ያነ​ዋ​ው​ጠ​ዋል፤ በነ​ፋ​ሱም ኀይል ይነ​ቀ​ላል። 5ቅር​ን​ጫ​ፎ​ች​ዋም ሳያ​ድጉ ይሰ​በ​ራሉ፥ ፍሬ​ያ​ቸ​ውም ለመ​ብል የማ​ይ​ሆን ከንቱ ጨርቋ ነው፤ ጊዜው አይ​ደ​ለ​ምና፥ ለመ​ብ​ላ​ትም አይ​ገ​ባ​ምና። 6ከክ​ፉ​ዎች ሰዎች መኝታ የሚ​ወ​ለዱ ልጆ​ችም በተ​መ​ረ​መሩ ጊዜ ለእ​ና​ትና አባ​ታ​ቸው ክፋት ምስ​ክ​ሮች ናቸው። 7ጻድቅ ሰው ግን ለመ​ሞት በደ​ረሰ ጊዜ በዕ​ረ​ፍት ይኖ​ራል።
8የሽ​ም​ግ​ልና ክብር በዕ​ድሜ ብዛት አይ​ደ​ለም፤ በዓ​መ​ታ​ትም ቍጥር የሚ​ቈ​ጠር አይ​ደ​ለም። 9ሽበ​ትስ የሰው ዕው​ቀቱ ነው፤ የሽ​ም​ግ​ል​ናም አክ​ሊሏ ያለ ነውር መኖር ነው። 10እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ የሚ​ያ​ሰኝ ሰው በእ​ርሱ ዘንድ የሚ​ወ​ደድ ይሆ​ናል፤ በኀ​ጢ​አ​ተ​ኞ​ችም መካ​ከል ሲኖር ይለ​ያል። 11ክፋ​ትም ዕው​ቀ​ቱን ሳት​ለ​ው​ጥ​በት፥ ይህም ባይ​ሆን ሐሰት ሰው​ነ​ቱን ሳታ​ስ​ት​በት ተነ​ጥቆ ይሄ​ዳል። 12የክ​ፋት ቅን​ዐት በጎ ሥራ​ዎ​ችን ያጠ​ፋ​ልና፥ የፈ​ቃድ ነዘ​ህ​ላ​ል​ነ​ትም የዋህ ልቡ​ናን ይለ​ው​ጣ​ልና። 13በጥ​ቂት ዘመ​ንም ቢሞት ረዥም ዓመ​ታ​ትን ጨር​ሷል። 14ነፍሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ አሰ​ኝ​ታ​ዋ​ለ​ችና፤ ስለ​ዚ​ህም ከክ​ፉ​ዎች መካ​ከል ተለ​ይቶ በች​ኮላ ሄደ። 15ልዩ የሆኑ ሰዎች ግን ይህን አይ​ተው ልብ አላ​ደ​ረ​ጉ​ትም፤ የዚ​ህ​ንም ትር​ጓሜ በል​ባ​ቸው አላ​ሳ​ደ​ሩ​ትም። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጸጋው ለጻ​ድ​ቃኑ ነውና የይ​ቅ​ር​ታው ጕብ​ኝ​ትም ለመ​ረ​ጣ​ቸው ሰዎች ነውና።
የቅ​ዱ​ሳን ድል አድ​ራ​ጊ​ነ​ትና የኃ​ጥ​ኣን ፍርድ
16ጻድቅ ሰው ከሞተ በኋላ በሕ​ይ​ወት ባሉ ክፉ​ዎች ላይ ይፈ​ር​ዳል። ጐል​ማሳ ሰውም ፈጥኖ በሚ​ሞ​ት​በት ጊዜ የዐ​መፃ ሽም​ግ​ልና ዕድ​ሜ​አ​ቸው በበዛ በክ​ፉ​ዎች ሰዎች ላይ ይፈ​ር​ዳል። 17ጠቢብ የሆነ የጻ​ድ​ቁን ሞት አይ​ተው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ እርሱ ምን እንደ መከረ፥ ወደ እር​ሱም ለምን እንደ ሰበ​ሰ​በው አያ​ስ​ተ​ው​ሉ​ምና። 18እር​ሱ​ንም አይ​ተው በእ​ርሱ ይጠ​ቃ​ቀ​ሳሉ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን በእ​ነ​ርሱ ይሥ​ቃል። 19ከዚ​ህም በኋላ ለጐ​ስ​ቋላ ሞት ይሆ​ናሉ፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ሙታን ለሚ​ሰ​ደ​ቡ​በት ስድብ ይሆ​ናሉ። ይቈ​ር​ጣ​ቸ​ዋ​ልና፥ ይሰ​ነ​ጥ​ቃ​ቸ​ዋ​ል​ምና፥ ቃልም ሳይ​ኖ​ራ​ቸው በፊ​ታ​ቸው የወ​ደቁ ሆነው ይገ​ኛሉ። ከመ​ሠ​ረ​ታ​ቸ​ውም ያነ​ዋ​ው​ጣ​ቸ​ዋል፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ እንደ ተፈ​ታች ምድር ይሆ​ናሉ፥ የተ​ጨ​ነ​ቁም ይሆ​ናሉ፤ መታ​ሰ​ቢ​ያ​ቸ​ውም ይጠ​ፋል። 20በፍ​ር​ሃ​ትም ሆነው በኀ​ጢ​ኣ​ታ​ቸው ለመ​ወ​ቀስ ይቀ​ር​ባሉ፤ ኀጢ​ኣ​ታ​ቸ​ውም በፊ​ታ​ቸው ተገ​ልጦ ይዘ​ል​ፋ​ቸ​ዋል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ