2 ነገሥት 4:3 - Compare All Versions
2 ነገሥት 4:3 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
እርሱም፥ “ሂጂና ከጎረቤቶችሽ ሁሉ ከውጭ ባዶ ማድጋዎችን ተዋሺ፤ አታሳንሻቸውም።
2 ነገሥት 4:3 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
ኤልሳዕም እንዲህ አላት፤ “እንግዲያው ሂጂና ከጎረቤቶችሽ ሁሉ ጥቂት ሳይሆን ብዙ ማድጋ ተዋሺ፤
2 ነገሥት 4:3 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
እርሱም “ሄደሽ ከጎረቤቶችሽ ሁሉ ከሜዳ ባዶ ማድጋዎችን ተዋሺ፤ አታሳንሻቸውም፤” አላት።
2 ነገሥት 4:3 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)
ኤልሳዕም እንዲህ አላት፦ “ወደ ጐረቤቶችሽ ሄደሽ ማግኘት የምትችዪውን ያኽል ባዶ ማድጋ ለምኚ፤
2 ነገሥት 4:3 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
ኤልሳዕም እንዲህ አላት፦ “ወደ ጐረቤቶችሽ ሄደሽ ማግኘት የምትችዪውን ያኽል ባዶ ማድጋ ለምኚ፤