2 ነገሥት 4:34 - Compare All Versions

2 ነገሥት 4:34 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

መጥ​ቶም በሕ​ፃኑ ላይ ተኛ፤ አፉ​ንም በአፉ፥ ዐይ​ኖ​ቹ​ንም በዐ​ይ​ኖቹ፥ እጆ​ቹ​ንም በእ​ጆቹ ላይ አድ​ርጎ ተጋ​ደ​መ​በት፤ የሕ​ፃ​ኑም ሰው​ነት ሞቀ።

2 ነገሥት 4:34 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

በዐልጋው ላይ ወጥቶም በልጁ ላይ ተጋደመና አፉን በአፉ፣ ዐይኑን በዐይኑ፣ እጁን በእጁ ላይ አደረገ። ሙሉ በሙሉ እንደተዘረጋበትም፣ የልጁ ሰውነት መሞቅ ጀመረ።

2 ነገሥት 4:34 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

መጥቶም በሕፃኑ ላይ ተኛ፤ አፉንም በአፉ፥ ዐይኑንም በዓይኑ፥ እጁንም በእጁ ላይ አድርጎ ተጋደመበት፤ የሕፃኑም ገላ ሞቀ።

2 ነገሥት 4:34 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

ከዚህም በኋላ አፉን ከአፉ፥ ዐይኖቹን ከዐይኖቹ፥ እጆቹን ከእጆቹ ጋር ገጥሞ በልጁ ሬሳ ላይ ተጋደመ፤ ኤልሳዕም ተዘርግቶ እንደ ተጋደመበት የልጁ ሰውነት መሞቅ ጀመረ።

2 ነገሥት 4:34 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

ከዚህም በኋላ አፉን ከአፉ፥ ዐይኖቹን ከዐይኖቹ፥ እጆቹን ከእጆቹ ጋር ገጥሞ በልጁ ሬሳ ላይ ተጋደመ፤ ኤልሳዕም ተዘርግቶ እንደ ተጋደመበት የልጁ ሰውነት መሞቅ ጀመረ።