2 ነገሥት 5:14 - Compare All Versions

2 ነገሥት 5:14 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

ንዕ​ማ​ንም ወረደ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰው ኤል​ሳዕ እንደ ተና​ገ​ረው በዮ​ር​ዳ​ኖስ ሰባት ጊዜ ተጠ​መቀ፤ ሰው​ነ​ቱም እንደ ገና እንደ ትንሽ ብላ​ቴና ሰው​ነት ሆኖ ተመ​ለሰ፤ ንጹ​ሕም ሆነ።

2 ነገሥት 5:14 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

ስለዚህ ንዕማን ወረደ፤ የእግዚአብሔር ሰው እንደ ነገረውም በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ፤ ሥጋውም እንደ ትንሽ ልጅ ሥጋ ሆነ፤ ነጻም።

2 ነገሥት 5:14 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

ወረደም፤ የእግዚአብሔርም ሰው እንደ ተናገረው በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ፤ ሥጋውም እንደ ገና እንደ ትንሽ ብላቴና ሥጋ ሆኖ ተመለሰ፤ ንጹሕም ሆነ።

2 ነገሥት 5:14 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

ስለዚህም ንዕማን የእግዚአብሔር ሰው ባዘዘው መሠረት ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወርዶ ሰባት ጊዜ በመነከር ታጠበ፤ ከበሽታውም ፈጽሞ ነጻ፤ ሥጋውም እንደ ትንሽ ልጅ ገላ በመታደስ ፍጹም ጤናማ ሆነ፤

2 ነገሥት 5:14 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

ስለዚህም ንዕማን የእግዚአብሔር ሰው ባዘዘው መሠረት ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወርዶ ሰባት ጊዜ በመነከር ታጠበ፤ ከበሽታውም ፈጽሞ ነጻ፤ ሥጋውም እንደ ትንሽ ልጅ ገላ በመታደስ ፍጹም ጤናማ ሆነ፤