መክብብ 5:19 - ሁሉንም ስሪቶች ያወዳድሩ

መክብብ 5:19 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

አምላክ ለሰው ባለጠግነትና ሀብት መስጠቱ፣ እንዲደሰትበትም ማስቻሉ፣ ዕጣውን እንዲቀበልና በሥራውም እንዲደሰት ማድረጉ፣ ይህ የአምላክ ስጦታ ነው።

መክብብ 5:19 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

እግዚአብሔር ለሰው ሀብትና ብልጽግናን መስጠቱ የደከመበትን ድርሻ አግኝቶ በመብላትና በመጠጣት ደስ እንዲለው ፈቅዶለት ነው፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው።

መክብብ 5:19 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሰው ሁሉ ባለ​ጠ​ግ​ነ​ት​ንና ሀብ​ትን መስ​ጠቱ፥ ከእ​ር​ስ​ዋም ይበ​ላና ዕድል ፈን​ታ​ውን ይወ​ስድ ዘንድ፥ በድ​ካ​ሙም ደስ ይለው ዘንድ ማሠ​ል​ጠኑ ይህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስጦታ ነው።

መክብብ 5:19 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ ባለጠግነትንና ሀብትን መስጠቱ፥ ከእርስዋም ይበላና እድል ፈንታውን ይወስድ ዘንድ በድካሙም ደስ ይለው ዘንድ ማሠልጠኑ፥ ይህ የእግዚአብሔር ስጦታ ነው።

መክብብ 5:19 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

እግዚአብሔር በልቡ ደስታን እስካኖረ ድረስ፥ እርሱ የሕይወቱን ዘመን እጅግም አያስብም።