ኢዮብ 15:15-16 - ሁሉንም ስሪቶች ያወዳድሩ

ኢዮብ 15:15-16 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

እነሆ፤ እግዚአብሔር በቅዱሳኑ እንኳ አይታመንም፤ ሰማያትም በርሱ ፊት ንጹሓን አይደሉም። ታዲያ፣ ክፋትን እንደ ውሃ የሚጠጣ፣ አስጸያፊና ርኩስ ሰውማ እንዴት ይታመን!

ኢዮብ 15:15-16 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

እግዚአብሔር በመላእክቱ ላይ እምነት የለውም፤ ሰማያት እንኳ በእርሱ ፊት ንጹሓን አይደሉም፤ የተበላሸና የረከሰ ኃጢአትንም እንደ ውሃ የሚጠጣ ሰውማ ምንኛ የባሰ ነው?

ኢዮብ 15:15-16 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

እነሆ፥ በቅ​ዱ​ሳኑ እንኳ አይ​ታ​መ​ንም፤ ሰማ​ይም በፊቱ ንጹሕ አይ​ደ​ለም። ይል​ቁ​ንስ አስ​ጸ​ያ​ፊና የረ​ከሰ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም እንደ ውኃ የሚ​ጠጣ ሰው ምንኛ ያንስ?

ኢዮብ 15:15-16 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

እነሆ፥ በቅዱሳኑ ስንኳ አይታመንም፥ ሰማያትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም። ይልቁንስ አስጸያፊና የረከሰ፥ ኃጢአትንም እንደ ውኃ የሚጠጣ ሰው ምንኛ ያንስ?

ኢዮብ 15:15-16 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

እነሆ፥ ቅዱሳኑን እንኳን አያምናቸውም፥ ሰማያትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም። ታዲያ አስጸያፊና የረከሰ፥ በደልን እንደ ውኃ የሚጠጣ ሰው ምንኛ ያንስ?!”