ኢዮብ 17:11-12 - ሁሉንም ስሪቶች ያወዳድሩ

ኢዮብ 17:11-12 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)

ዕድሜዬ ዐለቀ፤ ዕቅዴም ከሸፈ፤ የልቤም ሐሳብ ከንቱ ሆነ። እነዚህ ሰዎች ሌሊቱን ወደ ቀን ይለውጣሉ፤ ጨልሞም እያዩ፣ ‘ብርሃን ቀርቧል’ ይላሉ።

ኢዮብ 17:11-12 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)

“የዕድሜዬ ዘመን ተፈጽሞአል፤ ዕቅዴና የልቤ ምኞት ከንቱ ሆኖ ቀርቶአል። እነዚህ ሰዎች ሌሊቱን ቀን ነው ይላሉ፤ ብርሃኑን ደግሞ ሊጨልም ነው ይላሉ።

ኢዮብ 17:11-12 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))

“ዘመ​ኖች በጩ​ኸት አለቁ፤ የልቤ ሥርም ተቈ​ረጠ። ቀኑ ሌሊት ሆነ​ብኝ። ከጨ​ለ​ማ​ውም የተ​ነሣ ብር​ሃኑ አጭር ነው።

ኢዮብ 17:11-12 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))

ዕድሜዬ አለፈች፥ አሳቤና የልቤ መሣርያ ተቈረጠ። ሌሊቱን ወደ ቀን ይለውጣሉ፥ ብርሃኑም ወደ ጨለማ የቀረበ ይመስላቸዋል።

ኢዮብ 17:11-12 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))

ቀኖቼ አለፉ፥ ዕቅዴና የልቤ ምኞት ቀለጠ። ሌሊቱን ወደ ቀን ይለውጣሉ፥ ብርሃኑም ወደ ጨለማ የቀረበ ይመስላቸዋል።