ኢዮብ 8:20-21 - ሁሉንም ስሪቶች ያወዳድሩ
ኢዮብ 8:20-21 NASV (አዲሱ መደበኛ ትርጒም)
“እነሆ፤ እግዚአብሔር እንከን የሌለበትን ሰው አይጥልም፤ የክፉዎችንም እጅ አያበረታም፤ እንደ ገና አፍህን በሣቅ፣ ከንፈሮችህንም በእልልታ ይሞላል።
ያጋሩ
ኢዮብ 8 NASVኢዮብ 8:20-21 አማ05 (አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም)
“እግዚአብሔር ደጋግ ሰዎችን አይጥላቸውም፤ ክፉዎችንም አይረዳቸውም። ስለዚህ አንተንም በደስታ እንድትስቅና ‘እልል’ እንድትል ያደርግሃል።
ያጋሩ
ኢዮብ 8 አማ05ኢዮብ 8:20-21 አማ2000 (የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ))
እነሆ፥ እግዚአብሔር የዋሁን ሰው አይጥለውም፥ የኀጢኣተኞችንም እጅ አያበረታም። የዝንጉዎችንም መባ አይቀበልም። የቅኖችን አፍ ሳቅ ይሞላል፥ ከንፈሮቻቸውንም ምስጋና ይሞላል።
ያጋሩ
ኢዮብ 8 አማ2000ኢዮብ 8:20-21 አማ54 (መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት))
እነሆ፥ እግዚአብሔር ፍጹሙን ሰው አይጥለውም፥ የኃጢአተኞችንም እጅ አያበረታም። አፍህን እንደ ገና ሳቅ ይሞላል፥ ከንፈሮችህንም እልልታ ይሞላል።
ያጋሩ
ኢዮብ 8 አማ54ኢዮብ 8:20-21 መቅካእኤ (መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ))
“እነሆ፥ እግዚአብሔር ፍጹሙን ሰው አይጥለውም፥ የክፉዎችን እጅ አያበረታም። አፍህን እንደገና በሳቅ፥ ከንፈሮችህንም በእልልታ ይሞላዋል።
ያጋሩ
ኢዮብ 8 መቅካእኤ