መዝሙር 91
91
መዝሙር 91
1በልዑል መጠጊያ የሚኖር፣
በሁሉን ቻይ አምላክ#91፥1 በዕብራይስጥ ሻዳይ ማለት ነው። ጥላ ሥር ያድራል።
2 እግዚአብሔርን፣ “መጠጊያዬ፣ ምሽጌ፣
የምታመንብህ አምላኬ” እለዋለሁ።#91፥2 አንዳንድ ትርጕሞች ይላል ይላሉ።
3እርሱ ከዐዳኝ ወጥመድ፣
ከአሰቃቂ ቸነፈር ያድንሃልና።
4በላባዎቹ ይጋርድሃል፤
በክንፎቹ ሥር መሸሸጊያ ታገኛለህ፤
ታማኝነቱ ጋሻና መከታ ይሆንሃል።
5የሌሊትን አስደንጋጭነት፣
በቀን የሚወረወረውንም ፍላጻ አትፈራም፤
6በጨለማ የሚያደባ ቸነፈር፣
በቀትር ረፍራፊውም አያሠጋህም።
7በአጠገብህ ሺሕ፣ በቀኝህም ዐሥር ሺሕ ይወድቃል፤
ወደ አንተ ግን አይቀርብም።
8በዐይንህ ብቻ ትመለከታለህ፤
የክፉዎችንም መቀጣት ታያለህ።
9 “እግዚአብሔርን መሸሸጊያ፣”
ልዑልንም መጠጊያህ አድርገኸዋልና።
10ክፉ ነገር አያገኝህም፤
መቅሠፍትም ወደ ድንኳንህ አይገባም፤
11በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ፣
እግርህም ከድንጋይ ጋራ እንዳይሰናከል፤
12በእጆቻቸው ያነሡህ ዘንድ፣
መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዝልሃል።
13በአንበሳና በእፉኝት ላይ ትጫማለህ፤
ደቦሉን አንበሳና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
14“ወድዶኛልና እታደገዋለሁ፤
ስሜን ዐውቋልና እከልለዋለሁ።
15ይጠራኛል፤ እመልስለታለሁ፤
በመከራው ጊዜ ከርሱ ጋራ እሆናለሁ፤
አድነዋለሁ፤ አከብረዋለሁ።
16ረዥም ዕድሜን አጠግበዋለሁ፤
ማዳኔንም አሳየዋለሁ።”
Currently Selected:
መዝሙር 91: NASV
Highlight
Share
Copy
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapistaging.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fen.png&w=128&q=75)
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.