YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 93

93
መዝሙር 93
1 እግዚአብሔር ነገሠ፤ ግርማንም ተጐናጸፈ፤
እግዚአብሔር ግርማን ለበሰ፤
ብርታትንም ታጠቀ፤
ዓለም እንዳትናወጥ ጸንታለች፤
ማንም አይነቀንቃትም።
2ዙፋንህ ከጥንት ጀምሮ የጸና ነው፤
አንተም ከዘላለም እስከ ዘላለም አለህ።
3 እግዚአብሔር ሆይ፤ ወንዞች ከፍ አደረጉ፤
ወንዞች ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ፤
ወንዞች የሚያስገመግም ማዕበላቸውን ከፍ አደረጉ።
4ከብዙ ውሆች ድምፅ ይልቅ፣
ከባሕርም ሞገድ ይልቅ፣
ከፍ ብሎ ያለው እግዚአብሔር ኀያል ነው።
5ምስክርነትህ የጸና ነው፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ ዘላለሙ፣
ቤትህ በቅድስና ይዋባል።

Currently Selected:

መዝሙር 93: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in