መጽሐፈ መዝሙር 120
120
ከሐሰተኞችና ከአታላዮች ለመዳን የሚቀርብ ጸሎት
1መከራ በደረሰብኝ ጊዜ፥
ወደ እግዚአብሔር ጮኽኩ፤
እርሱም ሰማኝ።
2እግዚአብሔር ሆይ!
ከሐሰተኞችና ከአታላዮች አድነኝ።
3እናንተ አታላዮች!
እግዚአብሔር እናንተን ምን ቢያደርጋችሁ ይሻላል?
እንዴትስ ቢቀጣችሁ ይሻላል?
4በተሳለ የወታደር ፍላጻ ይወጋችኋል፤
በከሰል ፍምም ያቃጥላችኋል።
5በቄዳር ሕዝብ መካከል
በሜሼክ ስደተኛ ሆኜ በመኖሬ ወዮልኝ!
6ሰላምን ከሚጠሉ ሕዝቦች ጋር
እጅግ ለረጅም ጊዜ ኖርኩ።
7እኔ ሰላምን እደግፋለሁ፤
ስለ ሰላም በምናገርበት ጊዜ እነርሱ ስለ ጦርነት ያወራሉ።
Currently Selected:
መጽሐፈ መዝሙር 120: አማ05
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997
መጽሐፈ መዝሙር 120
120
ከሐሰተኞችና ከአታላዮች ለመዳን የሚቀርብ ጸሎት
1መከራ በደረሰብኝ ጊዜ፥
ወደ እግዚአብሔር ጮኽኩ፤
እርሱም ሰማኝ።
2እግዚአብሔር ሆይ!
ከሐሰተኞችና ከአታላዮች አድነኝ።
3እናንተ አታላዮች!
እግዚአብሔር እናንተን ምን ቢያደርጋችሁ ይሻላል?
እንዴትስ ቢቀጣችሁ ይሻላል?
4በተሳለ የወታደር ፍላጻ ይወጋችኋል፤
በከሰል ፍምም ያቃጥላችኋል።
5በቄዳር ሕዝብ መካከል
በሜሼክ ስደተኛ ሆኜ በመኖሬ ወዮልኝ!
6ሰላምን ከሚጠሉ ሕዝቦች ጋር
እጅግ ለረጅም ጊዜ ኖርኩ።
7እኔ ሰላምን እደግፋለሁ፤
ስለ ሰላም በምናገርበት ጊዜ እነርሱ ስለ ጦርነት ያወራሉ።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997