መዝሙረ ዳዊት 64
64
1ለመዘምራን አለቃ፥ የዳዊት መዝሙር።
2አቤቱ፥ በሮሮዬ ድምፄን ስማ፥
ከጠላትም ፍርሃት ነፍሴን አድን።
3ከክፉዎች ደባ፥
ከዓመፀኞችም ብዛት ሰውረኝ።
4 #
መዝ. 11፥2፤ 37፥14፤ 55፥22፤ 57፥5። እንደ ሰይፍ ምላሳቸውን አሰሉ፥
እንደ ፍላጻ መራራ ነገርን ለመወርወር፥
5ንጹሕንም በስውር ለመንደፍ ቀስትን ገተሩ፥
ድንገት ይነድፉታል አይፈሩምም።
6ለእነርሱ ለራሳቸው ክፉ ነገርን አጸኑ፥
ወጥመድን ይሰውሩ ዘንድ ተማከሩ፥
ማንስ ያየናል? ይላሉ።
7 #
መዝ. 140፥3፤ ምሳ. 6፥14። ዓመፃን ፈለጓት፥
ሲፈትኑም አለቁ፥
የሰው የውስጥ አሳቡና ልቡ የጠለቀ ነው፥
8 #
መዝ. 7፥13-14፤ 38፥3፤ ዘዳ. 32፥42። እግዚአብሔርም ከፍ ከፍ ይላል።
ድንገተኛ ፍላጻም ያቈስላቸዋል፥
9 #
መዝ. 5፥11፤ 44፥14፤ 52፥6። አንደበታቸው ያሰናክላቸዋል፥
የሚያዩአቸውም ሁሉ ይደነግጣሉ።
10ሰዎች ሁሉ ፈሩ፥
የእግዚአብሔርንም ሥራ ተናገሩ፥
ሥራውንም አስተዋሉ።
11 #
መዝ. 36፥8፤ 57፥2። ጻድቅ በጌታ ደስ ይለዋል፥ በእርሱም ይታመናል፥
ልባቸውም ቅን የሆነ ሁሉ እልል ይላሉ።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 64: መቅካእኤ
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መዝሙረ ዳዊት 64
64
1ለመዘምራን አለቃ፥ የዳዊት መዝሙር።
2አቤቱ፥ በሮሮዬ ድምፄን ስማ፥
ከጠላትም ፍርሃት ነፍሴን አድን።
3ከክፉዎች ደባ፥
ከዓመፀኞችም ብዛት ሰውረኝ።
4 #
መዝ. 11፥2፤ 37፥14፤ 55፥22፤ 57፥5። እንደ ሰይፍ ምላሳቸውን አሰሉ፥
እንደ ፍላጻ መራራ ነገርን ለመወርወር፥
5ንጹሕንም በስውር ለመንደፍ ቀስትን ገተሩ፥
ድንገት ይነድፉታል አይፈሩምም።
6ለእነርሱ ለራሳቸው ክፉ ነገርን አጸኑ፥
ወጥመድን ይሰውሩ ዘንድ ተማከሩ፥
ማንስ ያየናል? ይላሉ።
7 #
መዝ. 140፥3፤ ምሳ. 6፥14። ዓመፃን ፈለጓት፥
ሲፈትኑም አለቁ፥
የሰው የውስጥ አሳቡና ልቡ የጠለቀ ነው፥
8 #
መዝ. 7፥13-14፤ 38፥3፤ ዘዳ. 32፥42። እግዚአብሔርም ከፍ ከፍ ይላል።
ድንገተኛ ፍላጻም ያቈስላቸዋል፥
9 #
መዝ. 5፥11፤ 44፥14፤ 52፥6። አንደበታቸው ያሰናክላቸዋል፥
የሚያዩአቸውም ሁሉ ይደነግጣሉ።
10ሰዎች ሁሉ ፈሩ፥
የእግዚአብሔርንም ሥራ ተናገሩ፥
ሥራውንም አስተዋሉ።
11 #
መዝ. 36፥8፤ 57፥2። ጻድቅ በጌታ ደስ ይለዋል፥ በእርሱም ይታመናል፥
ልባቸውም ቅን የሆነ ሁሉ እልል ይላሉ።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in