መዝሙረ ዳዊት 95
95
የዳዊት ምስጋና መዝሙር
1ኑ፥ በጌታ ደስ ይበለን፥
ለመዳናችን ዓለት እልል እንበል።
2በምስጋና ወደ ፊቱ እንድረስ፥
በዝማሬም ለእርሱ እልል እንበል፥
3 #
መዝ. 47፥3፤ 135፥5። ጌታ ታላቅ አምላክ ነውና፥
በአማልክትም ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉሥ ነውና።
4የምድር ዳርቻዎችም በእጁ ውስጥ ናቸው፥
የተራሮች ከፍታዎች የእርሱ ናቸው።
5 #
መዝ. 24፥1-2። ባሕር የእርሱ ናት እርሱም ፈጠራት፥
የብስንም እጆቹ ሠሩአት።
6ኑ፥ እንስገድ ለእርሱም እንገዛ፥
በፈጠረን በእርሱ በጌታ ፊት እንበርከክ፥
7 #
መዝ. 81፥8፤ 106፥32፤ ዕብ. 3፥7-11፤15፤ 4፥3፤5፤7። እርሱ አምላካችን ነውና፥
እኛ የማሰማርያው ሕዝብ የእጁም በጎች ነንና።#መዝ. 23፥1-3፤ 100፥3፤ ሚክ. 7፥14።
8በምድረ በዳ፥ በመሪባና በማሳ#95፥8 የቦታ ስሞች እንዳደረጋችሁት፥
ልባችሁን አታጽኑ።
9 #
ዘኍ. 14፥22፤ 20፥2-13፤ ዘዳ. 6፥16፤ 33፥8። የተፈታተኑኝ አባቶቻችሁ
ምንም እንኳን ሥራዬን ቢያዩም ፈተኑኝ።
10 #
መዝ. 78፥8፤ ዘኍ. 14፥34፤ ዘዳ. 32፥5። ያችን ትውልድ አርባ ዓመት ተጸየፍኳት፦
ሁልጊዜ ልባቸው ይስታል፥
“እነርሱም መንገዴን አላወቁም” አልሁ።
11“ወደ ዕረፍቴም ጨርሶ አትገቡም” ስል በቁጣዬ ማልሁ።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 95: መቅካእኤ
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መዝሙረ ዳዊት 95
95
የዳዊት ምስጋና መዝሙር
1ኑ፥ በጌታ ደስ ይበለን፥
ለመዳናችን ዓለት እልል እንበል።
2በምስጋና ወደ ፊቱ እንድረስ፥
በዝማሬም ለእርሱ እልል እንበል፥
3 #
መዝ. 47፥3፤ 135፥5። ጌታ ታላቅ አምላክ ነውና፥
በአማልክትም ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉሥ ነውና።
4የምድር ዳርቻዎችም በእጁ ውስጥ ናቸው፥
የተራሮች ከፍታዎች የእርሱ ናቸው።
5 #
መዝ. 24፥1-2። ባሕር የእርሱ ናት እርሱም ፈጠራት፥
የብስንም እጆቹ ሠሩአት።
6ኑ፥ እንስገድ ለእርሱም እንገዛ፥
በፈጠረን በእርሱ በጌታ ፊት እንበርከክ፥
7 #
መዝ. 81፥8፤ 106፥32፤ ዕብ. 3፥7-11፤15፤ 4፥3፤5፤7። እርሱ አምላካችን ነውና፥
እኛ የማሰማርያው ሕዝብ የእጁም በጎች ነንና።#መዝ. 23፥1-3፤ 100፥3፤ ሚክ. 7፥14።
8በምድረ በዳ፥ በመሪባና በማሳ#95፥8 የቦታ ስሞች እንዳደረጋችሁት፥
ልባችሁን አታጽኑ።
9 #
ዘኍ. 14፥22፤ 20፥2-13፤ ዘዳ. 6፥16፤ 33፥8። የተፈታተኑኝ አባቶቻችሁ
ምንም እንኳን ሥራዬን ቢያዩም ፈተኑኝ።
10 #
መዝ. 78፥8፤ ዘኍ. 14፥34፤ ዘዳ. 32፥5። ያችን ትውልድ አርባ ዓመት ተጸየፍኳት፦
ሁልጊዜ ልባቸው ይስታል፥
“እነርሱም መንገዴን አላወቁም” አልሁ።
11“ወደ ዕረፍቴም ጨርሶ አትገቡም” ስል በቁጣዬ ማልሁ።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in