1
ኦሪት ዘፍጥረት 3:6
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደሆነ፥ ለዐይንም ለማየት እንደሚያስጐመጅ፥ መልካምንም እንደሚያሳውቅ ባየች ጊዜ፥ ከፍሬው ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው፤ እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።
مقایسه
ኦሪት ዘፍጥረት 3:6 را جستجو کنید
2
ኦሪት ዘፍጥረት 3:1
እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠራቸው ከምድር አራዊት ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበር። እባብም ሴቲቱን “እግዚአብሔር በገነት ካለው ዛፍ ሁሉ አትብሉ ያላችሁ ለምንድን ነው?” አላት።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:1 را جستجو کنید
3
ኦሪት ዘፍጥረት 3:15
በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፤ አንተም ሰኰናውን ትነድፋለህ።”
ኦሪት ዘፍጥረት 3:15 را جستجو کنید
4
ኦሪት ዘፍጥረት 3:16
ለሴቲቱም እግዚአብሔር አላት፥ “ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ከወለድሽም በኋላ ፈቃድሽ ወደ ባልሽ ይሆናል፤ እርሱም ይገዛሻል።”
ኦሪት ዘፍጥረት 3:16 را جستجو کنید
5
ኦሪት ዘፍጥረት 3:19
ወደ ወጣህበት መሬት እስክትመለስ ድረስ በፊትህ ወዝ እንጀራህን ትበላለህ፤ አፈር ነህና ወደ አፈርም ትመለሳለህና።”
ኦሪት ዘፍጥረት 3:19 را جستجو کنید
6
ኦሪት ዘፍጥረት 3:17
እግዚአብሔርም አዳምን አለው፥ “የሚስትህን ቃል ሰምተሃልና፥ ከእርሱ እንዳትበላ ከአዘዝሁህ ከዚያ ዛፍም በልተሃልና ምድር በሥራህ የተረገመች ትሁን፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ በድካም ከእርስዋ ትበላለህ፤
ኦሪት ዘፍጥረት 3:17 را جستجو کنید
7
ኦሪት ዘፍጥረት 3:11
እግዚአብሔርም አለው፥ “ዕራቁትህን እንደሆንህ ማን ነገረህ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን?”
ኦሪት ዘፍጥረት 3:11 را جستجو کنید
8
ኦሪት ዘፍጥረት 3:24
አዳምንም አስወጣው፤ ደስታ በሚገኝባት በገነት አንጻርም አኖረው፤ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በእጃቸው የያዙ ኪሩቤልን አዘዛቸው።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:24 را جستجو کنید
9
ኦሪት ዘፍጥረት 3:20
አዳምም ለሚስቱ “ሔዋን” ብሎ ስም አወጣ፤ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:20 را جستجو کنید
خانه
كتاب مقدس
برنامههای مطالعه
ویدیوها