1
የሉቃስ ወንጌል 13:24
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
“ወደ ጠባቡ በር ትገቡ ዘንድ በርቱ፤ እላችኋለሁ፥ ሊገቡ የሚሹ ብዙዎች ናቸው፤ ግን አይችሉም።
ប្រៀបធៀប
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:24
2
የሉቃስ ወንጌል 13:11-12
ዐሥራ ስምንት ዓመት ሙሉ ጋኔን ያጐበጣት አንዲት ሴት ነበረች፤ ጐባጣም ነበረች፤ ከቶ ቀጥ ብላ መቆም አትችልም ነበር። ጌታችን ኢየሱስም አይቶ ራራላት፥ ጠርቶም፥ “ሴትዮ፥ ከደዌሽ ተፈትተሻል” አላት።
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:11-12
3
የሉቃስ ወንጌል 13:13
እጁንም በላይዋ ጫነ፤ ያንጊዜም ፈጥና ቀጥ አለች፤ እግዚአብሔርንም አመሰገነችው።
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:13
4
የሉቃስ ወንጌል 13:30
ኋለኞች ፊተኞች ይሆናሉ፤ ፊተኞችም ኋለኞች ይሆናሉ።”
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:30
5
የሉቃስ ወንጌል 13:25
ባለቤቱ ተነሥቶ ደጁን ይዘጋልና፤ ያንጊዜ ከደጅ ቆመው፦ ‘አቤቱ፥ አቤቱ፥ ክፈትልን’ እያሉ በር ሊመቱ ይጀምራሉ፤ መልሶም፦ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም ይላቸዋል።
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:25
6
የሉቃስ ወንጌል 13:5
አይደለም፤ እላችኋለሁ፤ እናንተም ንስሓ ካልገባችሁ ሁላችሁ እንደ እነርሱ ትጠፋላችሁ።”
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:5
7
የሉቃስ ወንጌል 13:27
እርሱም እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ዐመፅን የምታደርጉ ሁላችሁ፥ ከእኔ ራቁ፤
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:27
8
የሉቃስ ወንጌል 13:18-19
በዚያ ቀንም ጌታችን ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፥ “መንግሥተ ሰማያት ምን ትመስላለች? በምንስ እመስላታለሁ? ሰው ወስዶ በእርሻ ውስጥ የዘራት የሰናፍጭ ቅንጣትን ትመስላለች፤ አደገች፤ ታላቅ ዛፍም ሆነች፤ የሰማይ ወፎችም በቅርንጫፎችዋ ውስጥ ተጠለሉ።”
រុករក የሉቃስ ወንጌል 13:18-19
ទំព័រដើម
ព្រះគម្ពីរ
គម្រោងអាន
វីដេអូ