1
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:17
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
በአንቺ ላይ የተሠራ መሣሪያ ሁሉ እንዲከናወን አላደርግም፤ በአንቺ ላይ ለፍርድ የሚነሣውን ድምፅ ሁሉ ታጠፊያለሽ፤ ጠላቶችሽም ሁሉ ይፈረድባቸዋል፤ እግዚአብሔርንም ለሚያገለግሉ ርስት አላቸው፤ ጻድቃኔም ትሆኑኛላችሁ ይላል እግዚአብሔር።
አወዳድር
{{ጥቅስ}} ያስሱ
2
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:10
ተራሮችን እንዳልቀሥፋቸው እንዳላፈልሳቸውም፥ ኮረብቶችም እንዳይነዋወጡ እንደ ማልሁ እንዲሁ ከእኔ ዘንድ ያለሽ ይቅርታ አያልቅም፤ የሰላምሽ ቃል ኪዳንም አይጠፋም፤ መሓሪሽ እግዚአብሔር ይህን ተናግሮአልና።
3
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:4
አታፍሪምና አትፍሪ፤ አቷረጂምና አትደንግጪ፤ የዘለዓለም እፍረትሽንም ትረሺዋለሽ፤ የመበለትነትሽንም ስድብ ከእንግዲህ ወዲህ አታስቢም።
4
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:5
ፈጣሪሽ እግዚአብሔር ነው፤ ስሙም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ የእስራኤልም አምላክ ታዳጊሽ ነው፤ እርሱም በምድር ሁሉ እንደዚሁ ይጠራል።
5
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:2
የድንኳንሽን ስፍራ አስፊ፤ መጋረጃዎችሽንም ዘርጊ፤ አትቈጥቢ፤ አውታሮችሽን አስረዝሚ፤ ካስሞችሽንም ትከዪ።
6
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:13
ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፤ ልጆችሽም በብዙ ሰላም ይኖራሉ።
7
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:8
በጥቂት ቍጣ ፊቴን ከአንቺ ሰወርሁ፤ በዘለዓለም ቸርነት ይቅር እልሻለሁ፥ ይላል ታዳጊሽ እግዚአብሔር።
8
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:7
ጥቂት ጊዜ ተውሁሽ፤ በታላቅ ምሕረትም ይቅር እልሻለሁ።
9
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:9
ከኖኅ ዘመን ውኃ ጀምሮ ይህ ለእኔ ምስክር ነው፤ ቀድሞ ከእንግዲህ ወዲህ ምድርን እንዳልቈጣት እንደ ማልሁ፥
10
ትንቢተ ኢሳይያስ 54:12
ግንብሽንም በቀይ ዕንቍ፥ በሮችሽንም ቢረሌ በተባለ ዕንቍ፥ ዳርቻዎችሽንም በከበረ ዕንቍ እሠራለሁ።
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች