መዝሙር 120

120
መዝሙር 120
መዝሙረ መዓርግ።
1በተጨነቅሁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ተጣራሁ፤
እርሱም መለሰልኝ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሐሰተኛ ከንፈር፣
ከአታላይ ምላስም አድነኝ።
3ሐሰተኛ አንደበት ሆይ፤ ምን ይከፈልህ?
ከዚህስ የባሰ ምን ይደረግብህ?
4በተሳለ የጦረኛ ቀስት፣
በግራር ከሰል ፍም ይቀጣሃል።
5በሜሼኽ እኖራለሁና፣
በቄዳር ድንኳኖች መካከል እቀመጣለሁና ወዮልኝ!
6ሰላምን በሚጠሉ መካከል፣
ነፍሴ እጅግ ብዙ ጊዜ ኖረች።
7እኔ የሰላም ሰው ነኝ፤
እነርሱ ግን በተናገርሁ ጊዜ ጦርነትን ይሻሉ።

Currently Selected:

መዝሙር 120: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ