መዝሙር 120
120
መዝሙር 120
መዝሙረ መዓርግ።
1በተጨነቅሁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ተጣራሁ፤
እርሱም መለሰልኝ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሐሰተኛ ከንፈር፣
ከአታላይ ምላስም አድነኝ።
3ሐሰተኛ አንደበት ሆይ፤ ምን ይከፈልህ?
ከዚህስ የባሰ ምን ይደረግብህ?
4በተሳለ የጦረኛ ቀስት፣
በግራር ከሰል ፍም ይቀጣሃል።
5በሜሼኽ እኖራለሁና፣
በቄዳር ድንኳኖች መካከል እቀመጣለሁና ወዮልኝ!
6ሰላምን በሚጠሉ መካከል፣
ነፍሴ እጅግ ብዙ ጊዜ ኖረች።
7እኔ የሰላም ሰው ነኝ፤
እነርሱ ግን በተናገርሁ ጊዜ ጦርነትን ይሻሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.