መዝሙር 129
129
መዝሙር 129
መዝሙረ መዓርግ።
1እስራኤል እንዲህ ይበል፦
“ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
2በርግጥ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
ዳሩ ግን ድል አላደረጉኝም።
3ዐራሾች ጀርባዬን ዐረሱት፤
ትልማቸውንም አስረዘሙት።”
4 እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ነው፤
የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለው።
5ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣
ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
6ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ፣
በጣራ ላይ እንደ በቀለ ሣር ይሁኑ፤
7ደግሞም ለዐጫጅ እጁን፣
ለነዶ ሰብሳቢ ዕቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።
8መንገድ ዐላፊዎችም፣
“የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤
በእግዚአብሔር ስም እንባርካችኋለን” አይበሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.
መዝሙር 129
129
መዝሙር 129
መዝሙረ መዓርግ።
1እስራኤል እንዲህ ይበል፦
“ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
2በርግጥ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
ዳሩ ግን ድል አላደረጉኝም።
3ዐራሾች ጀርባዬን ዐረሱት፤
ትልማቸውንም አስረዘሙት።”
4 እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ነው፤
የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለው።
5ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣
ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
6ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ፣
በጣራ ላይ እንደ በቀለ ሣር ይሁኑ፤
7ደግሞም ለዐጫጅ እጁን፣
ለነዶ ሰብሳቢ ዕቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።
8መንገድ ዐላፊዎችም፣
“የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤
በእግዚአብሔር ስም እንባርካችኋለን” አይበሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.