መዝሙር 130

130
መዝሙር 130
መዝሙረ መዓርግ።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጥልቅ ወደ አንተ እጮኻለሁ።
2ጌታ ሆይ፤ ድምፄን ስማ፤
ጆሮዎችህ የልመናዬን ቃል፣
የሚያዳምጡ ይሁኑ።
3 እግዚአብሔር ሆይ፤ ኀጢአትን ብትቈጣጠር፣
ጌታ ሆይ፤ ማን ሊቆም ይችላል?
4ነገር ግን በአንተ ዘንድ ይቅርታ አለ፤
ስለዚህም ልትፈራ ይገባሃል።
5 እግዚአብሔርን ደጅ እጠናለሁ፤ ነፍሴም በትዕግሥት ትጠብቀዋለች፤
በቃሉም ተስፋ አደርጋለሁ።
6ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣
አዎን፤ ዘብ ዐዳሪ ንጋትን ከሚጠባበቅ ይልቅ፣
ነፍሴ ጌታን ትጠባበቃለች።
7 በእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረት፣
በርሱም ዘንድ ማዳን አለና፣
እስራኤል ሆይ፤ በእግዚአብሔር ተስፋ አድርግ።
8እርሱም እስራኤልን፣
ከኀጢአቱ ሁሉ ያድነዋል።

Currently Selected:

መዝሙር 130: NASV

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ